የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአፋርና የሶማሌ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በሰመራ ከተማ የልማት ስራዎችን ጎበኙ

Mar 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦የአፋርና የሶማሌ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እንዲሁም የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በሰመራ ከተማ የልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ፣ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ፣ የሰላም ሚኒስትር መሀመድ ኢድሪስን ጨምሮ ሌሎች የክልልና የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በጉብኝቱ ተሳትፈዋል።


ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎቹ በጉብኝታቸው በሰመራ ከተማ እየተገነባ የሚገኝ የዳቦ ፋብሪካ እንዲሁም የጨው ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችንና የከተማው የኮሪደር ልማት እንቅስቃሴን ተመልክተዋል።


ትናንት ምሽት የአፋርና የሶማሌ ህዝቦችን አብሮነትና ትስስር ማጠናከርን ዓላማ ያደረገ የጋራ ኢፍጣር መርሃ ግብር በሰመራ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.