የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ምርምር እና ስልጠና ላይ አተኩሮ እየሰራ ነው

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፦ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ በአቅም ግንባታ ስልጠና እና ምርምር ላይ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ አስታወቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በክረምት መርኃ ግብር ብቻ ከ6 ሺ 500 ለሚልቁ መምህራን እና አመራሮች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መስጠቱ ተመላክቷል፡፡

ለትምህርት ጥራት መጓደል የትምህርት ዩኒቨርሲቲ አለመኖር እንደ ምክንያት ሲነሳ የቆየ ሲሆን ይህንኑ ችግር ለመቅረፍ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ተቋቁሞ ወደ ስራ ገብቷል፡፡

የኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ተልዕኮ ወስዶ ወደ ስራ ከገባ አንስቶ አመርቂ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

በዚህም የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት ባለፉት ጥቂት አመታት ውጤታማ ተግባራትን ማከናወኑን አስታውቀዋል፡፡

የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የመምህራንን እና የአመራሮችን አቅም ማሳደግ ወሳኝ በመሆኑ የእቅም ግንባታ ላይ አተኩሮ እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር ስር መምህራንን የሚያሰለጥኑ ባለሙያዎችን በስፋት እያስተማረ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመፈራረም የትምህርት ጥራትን የሚያረጋግጡ የምርምር ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ለአብነትም ከአዲስ አበባ፣ ከኦሮሚያ እና ከአፋር ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመፈራረም በርካታ የጥናትና የምርምር ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የጀመረው ስራ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን ባለድርሻ አካላት ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፡፡

የቀድሞው ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓም ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ሆኖ በአዋጅ ወደ ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ መቀየሩ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026