
ደሴ ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ) ፡- ወሎ ዩኒቨርሲቲ በተግባር ተኮር ትምህርት ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ከማፍራት ባለፈ በተለያዩ የምርምር ሥራዎች የህብረተሰቡን ችግር የሚያቃልሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲ - ኢንዱስትሪ ትስስር መድረክ ዛሬ በደሴ ከተማ ተካሂዷል፡፡

በመድረኩ ላይ የወሎ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት ሐዋ ወሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ተቋሙ ለተግባር ተኮር ትምህርት ትኩረት በመስጠት የትምህርት ጥራቱን ከማረጋገጥ ባለፈ በቴክኖሎጂ የበለጸገ ብቁና ተወዳዳሪ ትውልድ ለማፍራት በቅንጅት እየሰራ ይገኛል፡፡
ችግር ፈቺ ጥናትና ምርምር በማካሄድም የህብረተሰቡን ችግር በመፍታት ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመው፤ ወደ ተግባር የሚቀየሩ በርካታ ምርምሮች እየተሰሩ ነው ብለዋል፡፡
ለዚህም በአካባቢው ከሚገኙ ኢንዱስትሪዎችና ምርምር ተቋማት ጋር ጭምር ትስስር በመፍጠር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በዩኒቨርሲቲው የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማበረታታት ሥራ ፈጣሪ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ የምርምርና የማህበረሰብ ጉድኝነት ጉዳዮች ተጠባባቂ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሠራዊት ሀንዲሶ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመማር ማስተማር ሥራቸው በተጓዳኝ የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያደርጉ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም ከኢንዱስትሪዎች እና ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ጋር በማስተሳሰር የማህበረሰቡን ችግር ማቃለል እንዲችሉ፣ ሁለንተናዊ ምርታማነትን እንዲያሳድጉ ሪፎርም ጭምር ተሰርቶ እየተተገበረ ይገኛል ብለዋል፡፡
ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የሚማሩትን በተግባር በማሳየት በቂ እውቀትና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከዩኒቨርሲቲ ጋር ትስስር መፈጠሩን የተናገሩት ደግሞ በአማራ ክልል መንግስታዊ የልማት ድርጅት የሆነው የብረታብረት ኢንዱስትሪ ማሽን ቴክኖሎጂ ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ፋጡማ ይማም ናቸው፡፡

በዚህም የማሽኖችን ተግባርና አሰራር ተረድተው የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያደርጉ እየተደረገ ነው ፤ ከሥራ ጠባቂነት ሥራ ፈጣሪ መሆን እንዲችሉም ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ ነው ብለዋል፡፡
የኮምቦልቻ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ መኮንን በበኩላቸው፤ ከዩኒቨርሲቲው፣ ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ትስስር በመፍጠር የቴክኖሎጅ እውቀት ሽግግር እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በመድረኩ የዩኒቨርሲቲው፣ የዞን፣ የከተማ አስተዳደር፣ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እንዲሁም በአካባቢው የሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አመራር አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026