
መተማ፤ መጋቢት 9/2017(ኢዜአ)፡- በምዕራብ ጎንደር ዞን በሚገኙ ከተሞች ከ91 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተለያየ የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ አስታወቀ።
በዞኑ መተማ ዮሐንስ ከተማ አስተዳደር እየተገነቡ ያሉ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችና ሌሎች የመሰረተ ልማት ግንባታዎች በክልሉና በዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ተጎብኝተዋል።
የዞኑ ከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ይግለጥ አበባው በጉብኝቱ ወቅት እንዳሉት የመሰረተ ልማት ግንባታው እየተካሄደ የሚገኘው በሶስት ከተማ አስተዳደሮችና አራት መሪ ማዘጋጃ ቤቶች ነው።
በከተሞቹ በህዝብ የሚነሱ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ በተደረገ ጥረት ከክልሉ መንግስት፣ ከህብረተሰቡና ከከተሞቹ በተሰበሰበ 91 ሚሊዮን 75 ሺህ ብር የ24 ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተካሄደ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

እየተገነቡ ከሚገኙት መካከልም የጌጠኛ ድንጋይ ንጣፍ፣ የውስጥ ለውስጥ ጠጠር መንገድ፣ አነስተኛ ድልድዮች፣ ዲቾችና የወጣቶች መዝናኛ ማዕከላት ይገኙበታል ብለዋል።
እየተገነቡ ባሉ መሰረተ ልማት ህብረተሰቡ በገንዘብና በጉልበት ከስድስት ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።
በእለቱ ከተጎበኙት ፕሮጀክቶች በመተማ ዮሃንስ ከተማ የተገነባው ከአራት ነጥብ አንድ ኪሎ ሜትር በላይ የውስጥ ለውስጥ የጠጠር መንገድ የህብረተሰቡን ችግር የቀረፈ መሆኑን ማየት ተችሏል ብለዋል።
የአማራ ህዝብ ታሪክ ማዕከል ኃላፊ አቶ አዲሱ በየነ በበኩላቸው ህብረተሰቡን ግንባር ቀደም ተሳታፊ በማድረግ የከተማዋን እድገት ለማፋጠን መትጋት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የህዝቡን የመልማት ጥያቄ ለመመለስ የተጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ለማስቀጠል አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግም ተናግረዋል።
የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪ አቶ ግዛቸው አስማማው እንደተናገሩት ከተማዋ የክልሉ ቀደምት ደረቅ ወደብ ብትሆንም የተሟላ ፕላን የሌላት በመሆኑ ማደግ ባለባት ልክ አላደገችም ብለዋል።
አሁን ላይ በከተማዋ የውስጥ ለውስጥ መንገድ እውን ለማድረግ የከተማዋ ህዝብ ያለምንም ካሳ ቤት በማፍረስ ልማቱ እንዲሳለጥ የድርሻቸውን መወጣቱ ይበል የሚያሰኝ ነው ያሉት።
"የሬሳ መውጫ አጥተን የምንቸገርበት ጊዜ ነበር" ያሉት ነዋሪው አሁን ላይ ግን መንገድ መከፈቱ የነዋሪውን ችግር ከማቃለሉም ባሻገር ለከተማዋ ውበት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በጉብኝቱ ላይም የዞን ከፍተኛ አመራር አባላትና የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026