የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ የልማት ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ገለጹ

Mar 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ በልማት መስክ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር በማስፋት ያላቸውን አጋርነት ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ።

የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ ከተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታዋ ዴንማርክ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ጨምሮ ያላት የልማት ትብብር ከኢትዮጵያ የቅድሚያ የትኩረት መስኮች ጋር የተናበቡ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ የመጣውን የልማት እርዳታ ፈተና ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ ፕሮግራሞችን በጋራ ፋይናንስ ማድረግ እና የረጅም ጊዜ ዘለቄታቸውን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የመንግስትን የፋይናንስ ግልጸኝነት ከማረጋገጥ ጥረቶች ጋር ተዳምሮ በተለያዩ ዘርፎች ለውጦች እንዲመጣ ማድረጉን አመልክተዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ጉምሩክ እና የታክስ አስተዳደር ለውጥ ከመጠባቸው ዘርፎች መካከል ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል።

በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ የዴንማርክ የልማት ፕሮግራሞች ከኢትዮጵያ ፍላጎቶች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን አመልክተዋል።

ዴንማርክ በቀጣይ ለኢትዮጵያ በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ ድጋፍ እንደምታደርግ ጠቁመዋል።

ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ ያላቸውን ጠንካራ እና ፍሬያማ አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

ዴንማርክ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የምታደርገውን አዲስ የልማት ፕሮግራም እ.አ.አ ጁን ወር 2025 ላይ እንደምታፀድቅ ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026