
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ በልማት መስክ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር በማስፋት ያላቸውን አጋርነት ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ ከተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ ዴንማርክ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ጨምሮ ያላት የልማት ትብብር ከኢትዮጵያ የቅድሚያ የትኩረት መስኮች ጋር የተናበቡ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ የመጣውን የልማት እርዳታ ፈተና ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ ፕሮግራሞችን በጋራ ፋይናንስ ማድረግ እና የረጅም ጊዜ ዘለቄታቸውን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የመንግስትን የፋይናንስ ግልጸኝነት ከማረጋገጥ ጥረቶች ጋር ተዳምሮ በተለያዩ ዘርፎች ለውጦች እንዲመጣ ማድረጉን አመልክተዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ጉምሩክ እና የታክስ አስተዳደር ለውጥ ከመጠባቸው ዘርፎች መካከል ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ የዴንማርክ የልማት ፕሮግራሞች ከኢትዮጵያ ፍላጎቶች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ዴንማርክ በቀጣይ ለኢትዮጵያ በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ ድጋፍ እንደምታደርግ ጠቁመዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ ያላቸውን ጠንካራ እና ፍሬያማ አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ዴንማርክ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የምታደርገውን አዲስ የልማት ፕሮግራም እ.አ.አ ጁን ወር 2025 ላይ እንደምታፀድቅ ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026