
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 9/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ በልማት መስክ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር በማስፋት ያላቸውን አጋርነት ለማጎልበት እንደሚሰሩ አስታወቁ።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ ከተመራ ልዑክ ጋር ተወያይተዋል።
ሚኒስትር ዴኤታዋ ዴንማርክ ማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ጨምሮ ያላት የልማት ትብብር ከኢትዮጵያ የቅድሚያ የትኩረት መስኮች ጋር የተናበቡ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ደረጃ እየቀነሰ የመጣውን የልማት እርዳታ ፈተና ከግምት ውስጥ ባስገባ ሁኔታ ፕሮግራሞችን በጋራ ፋይናንስ ማድረግ እና የረጅም ጊዜ ዘለቄታቸውን ማረጋገጥ ላይ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል ሚኒስትር ዴኤታዋ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የመንግስትን የፋይናንስ ግልጸኝነት ከማረጋገጥ ጥረቶች ጋር ተዳምሮ በተለያዩ ዘርፎች ለውጦች እንዲመጣ ማድረጉን አመልክተዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ጉምሩክ እና የታክስ አስተዳደር ለውጥ ከመጠባቸው ዘርፎች መካከል ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው ብለዋል።
በኢትዮጵያ የዴንማርክ አምባሳደር ሱኔ ክሮግስትሮፕ የዴንማርክ የልማት ፕሮግራሞች ከኢትዮጵያ ፍላጎቶች ጋር የተጣጣሙ መሆናቸውን አመልክተዋል።
ዴንማርክ በቀጣይ ለኢትዮጵያ በዘላቂ ልማት ላይ ያተኮረ ድጋፍ እንደምታደርግ ጠቁመዋል።
ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው ኢትዮጵያ እና ዴንማርክ ያላቸውን ጠንካራ እና ፍሬያማ አጋርነት ለማጠናከር በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።
ዴንማርክ በኢትዮጵያ ተግባራዊ የምታደርገውን አዲስ የልማት ፕሮግራም እ.አ.አ ጁን ወር 2025 ላይ እንደምታፀድቅ ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026