የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል

Mar 20, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤መጋቢት 10/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ አስገነዘቡ።


በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ በሚስተዋሉ ችግሮች ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላትና የዘርፉ ባለድርሻዎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።


ርዕሰ መስተዳድሯ፥በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እያደረጉ ነው።


ችግሮቹን ለመፍታት የዘርፉ አመራር አካላትና ባለድርሻዎች በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።


ለችግሩ አስተዋፆ ባላቸው አካላት ላይ አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቀዋል።


ርዕሰ መስተዳድሯ፥ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ተከታትሎ እርምት የሚወስድ ግብረ ሃይል እንዲቋቋምና በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።


በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላትና የዘርፉ ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026