
ጋምቤላ፤መጋቢት 10/2017 (ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አለሚቱ ኡሞድ አስገነዘቡ።
በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ በሚስተዋሉ ችግሮች ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላትና የዘርፉ ባለድርሻዎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።
ርዕሰ መስተዳድሯ፥በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ብልሹ አሰራሮች የነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እያደረጉ ነው።
ችግሮቹን ለመፍታት የዘርፉ አመራር አካላትና ባለድርሻዎች በትብብር ሊሰሩ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
ለችግሩ አስተዋፆ ባላቸው አካላት ላይ አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታውቀዋል።
ርዕሰ መስተዳድሯ፥ በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ዙሪያ የሚስተዋሉ ችግሮችን ተከታትሎ እርምት የሚወስድ ግብረ ሃይል እንዲቋቋምና በፍጥነት ወደ ስራ እንዲገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አካላትና የዘርፉ ባለድርሻዎች ተሳትፈዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026