የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የሸማቹን መብት በሚጥሱ ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ)፦ የሸማቹን መብት ለማስጠበቅ ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በተጨማሪ መብት ጥሰው በተገኙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገለጸ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ42ኛ ጊዜ የሚከበረው የሸማቾች ቀን በኢትዮጵያ ለ12ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ተከብሯል።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የአገር ውስጥ ንግድና ሸማቾች ጥበቃ መሪ ስራ አስፈጻሚ ሊቁ በነበሩ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የሸማቹ መብት በተለያየ መንገድ የሚጣስበት ሁኔታ አለ፡፡

ሸማቹ መብቱን እንዲያውቅ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች በተከታታይ ዓመታት በትኩረት እየተሰራበት እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡

በዚህ ዓመት ብቻ ከስምንት ሚሊዮን በላይ ለሆኑ ነዋሪዎች የሸማቾች መብትን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱን ለአብነት አንስተዋል፡፡

የሸማቹን መብት የሚጥሱ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እና ህጋዊ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ አንስተው በበጀት አመቱ ሰባት ወራት ብቻ ከ 109ሺ በላይ ነጋዴዎች ላይ የተለያዩ እርምጃዎች መወሰዳቸውን አስታውቀዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ኃላፊ ሀቢባ ሲራጅ በበኩላቸው፤ የሸማቾች መብት እንዲጠበቅ ከማድረግ አኳያ በከተማ አስተዳደሩ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰዋል።

ሸማቹ በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያለው ምርት እንዲያገኝ እንዲሁም ጊዜ ካለፈባቸው ምርቶች እንዲጠበቅ የማድረግ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል።

ይህም ቢሆን ግን ከችግሩ አኳያ ሰፊ ስራ የሚጠይቅ መሆኑን አንስተው፤ በቀጣይ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ሌሎች ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ጥበቃ ማህበር ፕሬዚዳንት ፈታኑር አህመድ በበኩላቸው እንደገለጹት፤ ለሸማቹ ግንዛቤ ከማስጨበጥ በተጨማሪ መብቱን የማያከብሩ ነጋዴዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.