
አሶሳ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከበጋ መስኖ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥በክልሉ ዘንድሮ በበጋ መስኖ 59 ሺህ ሄክታር ማሳን በማልማት 13 ሚሊዮን ኩንታል ለማምረት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።
የመስኖ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ የባለሙያ እገዛና 30 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጥረት መደረጉን አክለዋል።
እስካሁን ከለማው መሬት 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታውቀዋል።
ቀደም ሲል አርሶአደሩ የዝናብ ወቅትን በመጠበቅ ብቻ የሚያመርትበትን አሰራር በመቀየር በበጋ መስኖ ልማት ከሁለት ጊዜ በላይ በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩ በበጋ መስኖ ሽንኩርት፣ቲማቲም ፣ድንች፣ ጎመንና ሌሎችንም የአትክልት ዓይነቶች በስፋት በማምረት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በክልሉ ካሉ ትልልቅ ወንዞች ውሃ በመሳብና ቴክኖሎጂ በመጠቀም ከአርሶአደሩ በተጨማሪ ባለሃብቶች በበጋ መስኖ መሰማራታቸውን አቶ ባበክር ተናግረዋል።
ይህም የአርሶ አደሩን የስራ ባህል የቀየረ እና የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘንድሮ በበጋ መስኖ ለማልማት የታቀደውን ለማሳካት ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ተመልክቷል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026