የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከበጋ መስኖ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ተገኝቷል

Mar 20, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከበጋ መስኖ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥በክልሉ ዘንድሮ በበጋ መስኖ 59 ሺህ ሄክታር ማሳን በማልማት 13 ሚሊዮን ኩንታል ለማምረት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።

የመስኖ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ የባለሙያ እገዛና 30 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጥረት መደረጉን አክለዋል።

እስካሁን ከለማው መሬት 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታውቀዋል።

ቀደም ሲል አርሶአደሩ የዝናብ ወቅትን በመጠበቅ ብቻ የሚያመርትበትን አሰራር በመቀየር በበጋ መስኖ ልማት ከሁለት ጊዜ በላይ በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።

አርሶ አደሩ በበጋ መስኖ ሽንኩርት፣ቲማቲም ፣ድንች፣ ጎመንና ሌሎችንም የአትክልት ዓይነቶች በስፋት በማምረት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በክልሉ ካሉ ትልልቅ ወንዞች ውሃ በመሳብና ቴክኖሎጂ በመጠቀም ከአርሶአደሩ በተጨማሪ ባለሃብቶች በበጋ መስኖ መሰማራታቸውን አቶ ባበክር ተናግረዋል።

ይህም የአርሶ አደሩን የስራ ባህል የቀየረ እና የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘንድሮ በበጋ መስኖ ለማልማት የታቀደውን ለማሳካት ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.