
አሶሳ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከበጋ መስኖ 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ ለኢዜአ እንደተናገሩት፥በክልሉ ዘንድሮ በበጋ መስኖ 59 ሺህ ሄክታር ማሳን በማልማት 13 ሚሊዮን ኩንታል ለማምረት ታቅዶ ወደ ተግባር ተገብቷል።
የመስኖ ልማቱን ውጤታማ ለማድረግ የባለሙያ እገዛና 30 ሺህ ኩንታል ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ በማሰራጨት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጥረት መደረጉን አክለዋል።
እስካሁን ከለማው መሬት 5 ሚሊዮን ኩንታል ምርት መገኘቱን አስታውቀዋል።
ቀደም ሲል አርሶአደሩ የዝናብ ወቅትን በመጠበቅ ብቻ የሚያመርትበትን አሰራር በመቀየር በበጋ መስኖ ልማት ከሁለት ጊዜ በላይ በማልማት ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩ በበጋ መስኖ ሽንኩርት፣ቲማቲም ፣ድንች፣ ጎመንና ሌሎችንም የአትክልት ዓይነቶች በስፋት በማምረት ተጠቃሚ በመሆን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በክልሉ ካሉ ትልልቅ ወንዞች ውሃ በመሳብና ቴክኖሎጂ በመጠቀም ከአርሶአደሩ በተጨማሪ ባለሃብቶች በበጋ መስኖ መሰማራታቸውን አቶ ባበክር ተናግረዋል።
ይህም የአርሶ አደሩን የስራ ባህል የቀየረ እና የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዘንድሮ በበጋ መስኖ ለማልማት የታቀደውን ለማሳካት ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ተመልክቷል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026