
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ።
በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በሮም መቀመጫቸውን ያደረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች ቋሚ ተጠሪ ደሚቱ ሃምቢሳ ከዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ረዳት ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፋይናንስ ኦፕሬሽን ዲፓርትመንት ኃላፊ ሀርናን ዳነሪ አልቫራዶ ጋር ዛሬ በሮም ተወያይተዋል።
አምባሳደር ደሚቱ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋት፣ የመስኖ ልማት እና ሌሎች የግብርና ዘርፎች ውጤታማ ስራ ማከናወኗን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ረዳት ምክትል ፕሬዝዳንት ሀርናን ዳነሪ አልቫራዶ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ውጤት የሚደነቅ እና ለአፍሪካ እና ሌሎች ዓለም አገራት እንደ ተሞክሮ የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ፈንዱ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ አገራት በአነስተኛ ማሳ ይዞታ ላይ ተመሰርተው የግብርና ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ እና የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርና ለመገንባት እያደረጉ ያለውን ጥረት የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026