
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2017(ኢዜአ):- የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለፀ።
በጣሊያን የኢትዮጵያ አምባሳደር እና በሮም መቀመጫቸውን ያደረጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች ቋሚ ተጠሪ ደሚቱ ሃምቢሳ ከዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ረዳት ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፋይናንስ ኦፕሬሽን ዲፓርትመንት ኃላፊ ሀርናን ዳነሪ አልቫራዶ ጋር ዛሬ በሮም ተወያይተዋል።
አምባሳደር ደሚቱ ኢትዮጵያ በስንዴ ምርት፣ በአረንጓዴ አሻራ፣ በሌማት ትሩፋት፣ የመስኖ ልማት እና ሌሎች የግብርና ዘርፎች ውጤታማ ስራ ማከናወኗን ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ለኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ ረዳት ምክትል ፕሬዝዳንት ሀርናን ዳነሪ አልቫራዶ በበኩላቸው በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያስመዘገበች ያለችው ውጤት የሚደነቅ እና ለአፍሪካ እና ሌሎች ዓለም አገራት እንደ ተሞክሮ የሚወሰድ መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ፈንዱ ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል መናገራቸውን በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
የዓለም አቀፍ የግብርና ልማት ፈንድ አገራት በአነስተኛ ማሳ ይዞታ ላይ ተመሰርተው የግብርና ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ እና የአየር ንብረት ለውጥ የሚቋቋም ግብርና ለመገንባት እያደረጉ ያለውን ጥረት የሚደግፍ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026