የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በሐረሪ ክልል ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥን ውጤታማ ማድረግ ተችሏል

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በሚገኙ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ውጤታማና ተደራሽነትን ማድረግ መቻሉን የክልሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ አስታወቀ።


የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም በሰጡት መግለጫ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፉን ማሳደግ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።


በዚህም ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ውጤታማና ተደራሽ የማድረግ ስራዎች በትኩረት እየተሰራባቸው ነው ብለዋል።


በተለይ ከለውጡ በፊት የነበሩ አሳሪ ህጎችን በማሻሻልና ለዘርፉ እድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ፖሊሲዎችን በማውጣት ዘርፉን የማዘመንና ከጊዜው ጋር መራመድ የሚያስችል አሰራር መገንባት መቻሉንም አመልክተዋል።


በዚህም የመንግስት ተቋማት የደንበኞችና የተቋማት የመረጃ (ሰነድ) አያያዝን በዲጂታል በመቀየር ደህንነቱ የተጠበቀ ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እገዛ ማድረጉንም ነው የተናገሩት።


የመንግስት አገልግሎት መስጫዎችን ወደ አንድ ቋት በማስገባት ሀሰተኛ ሰነድ እና የመረጃ ማጭበርበር ችግሮችን ለመከላከል መቻሉን አስረድተዋል።


በቀጣይም መንግስት ሊገነባው ላቀደው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማዘመን በትኩረት እንደሚሰራ አቶ ጀማል መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.