
አዲስ አበባ ፤መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በሚገኙ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ውጤታማና ተደራሽነትን ማድረግ መቻሉን የክልሉ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ኃላፊ አቶ ጀማል ኢብራሂም በሰጡት መግለጫ ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት መንግስት ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ዘርፉን ማሳደግ አንዱ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ውጤታማና ተደራሽ የማድረግ ስራዎች በትኩረት እየተሰራባቸው ነው ብለዋል።
በተለይ ከለውጡ በፊት የነበሩ አሳሪ ህጎችን በማሻሻልና ለዘርፉ እድገት አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ፖሊሲዎችን በማውጣት ዘርፉን የማዘመንና ከጊዜው ጋር መራመድ የሚያስችል አሰራር መገንባት መቻሉንም አመልክተዋል።
በዚህም የመንግስት ተቋማት የደንበኞችና የተቋማት የመረጃ (ሰነድ) አያያዝን በዲጂታል በመቀየር ደህንነቱ የተጠበቀ ግልጽና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እገዛ ማድረጉንም ነው የተናገሩት።
የመንግስት አገልግሎት መስጫዎችን ወደ አንድ ቋት በማስገባት ሀሰተኛ ሰነድ እና የመረጃ ማጭበርበር ችግሮችን ለመከላከል መቻሉን አስረድተዋል።
በቀጣይም መንግስት ሊገነባው ላቀደው የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማዘመን በትኩረት እንደሚሰራ አቶ ጀማል መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026