
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ በማያቋርጥ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።
ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ወደ አገልግሎት የገቡት 100 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶቢሶች ጠዋትና ማታ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ያለውን የትራንስፖርት ሰልፍ እና የህዝብ እንግልት የሚቀንሱ ናቸው ብለዋል።
መንግስት ያወጣውን የአየር ብክለት የመከላከል ፖሊሲን በተሟላ ሁኔታ መተግበር ብሎም በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገባውን ነዳጅና የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ አውቶቢሶቹ የዲጂታል የትኬት ስርዓትን ተግባራዊ የሚያደርጉ፣ ዲጅታል ባስ ካርድ ሥርዓት (Bus Card System) እውን የሚያደርጉ፣ በካሜራ እና ጂፒኤስ ድጋፍ እና ቁጥጥር የሚደረግባቸው እንዲሁም ሃገር ውስጥ የበለፀገ ሲስተም እንደተገጠመላቸው አመልክተዋል።
የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሳለጥ እና ጥራትና ፈጣን የሆነ አገልግሎት ለህዝብ ለመስጠት ከለውጥ በፊት የነበረውን የአውቶቢስ ቁጥር በእጥፍ መጨመሩን ጠቁመዋል።
ከለውጡ በፊት ከ20 በመቶ በታች የነበረውን የመንገድ ሽፋን በ10 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉንም አስረድተዋል።

ተርሚናሎችን እና የመኪና ማቆሚያዎችን በ10 እጥፍ ማሳደግ የቻልንበት መሰረታዊ ለውጥ መጋቢት 24 የተጀመረው ለውጥ ያመጣው መሰረታዊ ውጤት ነው ብለዋል ከንቲባዋ።
ዛሬ የግል ኦፕሬተር ወደ ስራ መግባቱ በአሰራር እና በአገልግሎት ላይ አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ስራ በማስገባት የበለጠ ህዝቡን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ያለንን ቁርጠኝነት ያሳየንበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026