የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

አዲስ አበባ በማያቋርጥ የለውጥ ጎዳና ላይ ናት - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- አዲስ አበባ በማያቋርጥ የለውጥ ጎዳና ላይ እንደምትገኝ የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ዛሬ ወደ አገልግሎት የገቡት 100 ዘመናዊ የኤሌክትሪክ አውቶቢሶች ጠዋትና ማታ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ያለውን የትራንስፖርት ሰልፍ እና የህዝብ እንግልት የሚቀንሱ ናቸው ብለዋል።

መንግስት ያወጣውን የአየር ብክለት የመከላከል ፖሊሲን በተሟላ ሁኔታ መተግበር ብሎም በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚገባውን ነዳጅና የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስ የሚረዱ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የኤሌክትሪክ አውቶቢሶቹ የዲጂታል የትኬት ስርዓትን ተግባራዊ የሚያደርጉ፣ ዲጅታል ባስ ካርድ ሥርዓት (Bus Card System) እውን የሚያደርጉ፣ በካሜራ እና ጂፒኤስ ድጋፍ እና ቁጥጥር የሚደረግባቸው እንዲሁም ሃገር ውስጥ የበለፀገ ሲስተም እንደተገጠመላቸው አመልክተዋል።

የትራንስፖርት አገልግሎትን ለማሳለጥ እና ጥራትና ፈጣን የሆነ አገልግሎት ለህዝብ ለመስጠት ከለውጥ በፊት የነበረውን የአውቶቢስ ቁጥር በእጥፍ መጨመሩን ጠቁመዋል።

ከለውጡ በፊት ከ20 በመቶ በታች የነበረውን የመንገድ ሽፋን በ10 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉንም አስረድተዋል።


ተርሚናሎችን እና የመኪና ማቆሚያዎችን በ10 እጥፍ ማሳደግ የቻልንበት መሰረታዊ ለውጥ መጋቢት 24 የተጀመረው ለውጥ ያመጣው መሰረታዊ ውጤት ነው ብለዋል ከንቲባዋ።

ዛሬ የግል ኦፕሬተር ወደ ስራ መግባቱ በአሰራር እና በአገልግሎት ላይ አዳዲስ አሰራሮችን ወደ ስራ በማስገባት የበለጠ ህዝቡን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ያለንን ቁርጠኝነት ያሳየንበት ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026