የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በወልድያ ከተማ የኮሪደር ልማት እየተፋጠነ ነው

Apr 3, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ የሚገነባው የ16 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።

በከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሃመድ-ሷሊህ ያሲን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማት ስራው ከተማዋን ማዘመን የሚያስችል ነው።

የኮሪደር ልማቱ ከጀነቶ በር - ሸህ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ አደባባይ-ስታዲየም- እቴጌ መናፈሻ- ከአዳጎ አደባባይ- ጎንደር በር አድርጎ በፒያሳ እስከ ጉቦ በር የ16 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መሆኑን ተናግረዋል።

በ117 ሚሊዮን ብር በጀት የሚገነባው ከአዳጎ አደባባይ - ሙጋድ እስከ ጎንደር በር አደባባይ ያለው የ1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ያለውን የኮሪደር ልማት ዘንድሮ ለማጠናቀቅ ስራው እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህ የኮሪደር ልማትም ለ200 ሰዎች አዲስ የስራ እድል የፈጠረላቸው መሆኑን ጠቁመው፤ መላው የከተማው ህዝብ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጠል መልዕክት አስተላልፈዋል ።

ከወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች መካከለ አቶ ፍስሃ አያሌው በሰጡት አስተያየት፤ ተወልደው ያደጉባት ጥንታዊት የወልዲያ ከተማ በኮሪደር ልማቱ ገጽታዋ እየተቀየረ መምጣቱን ገልጸዋል።

በከተማዋ ባለው ጠባብ መንገድ እሰከ ዛሬ ተሽከርካሪዎችና እግረኞች በመጋፋት ለአደጋ እየተገለጥን ነበር ያሉት ነዋሪው፤ አሁን ላይ እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ይሄን መሰረታዊ ችግር የሚፈታ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የስራ እድል አግኝተንበት ቤተሰባችንን እየመራን ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026