
ወልዲያ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ የሚገነባው የ16 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ስራ እየተፋጠነ መሆኑን የከተማዋ አስተዳደር አስታወቀ።
በከተማ አስተዳደሩ የከተማና መሰረተ ልማት መምሪያ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሙሃመድ-ሷሊህ ያሲን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኮሪደር ልማት ስራው ከተማዋን ማዘመን የሚያስችል ነው።
የኮሪደር ልማቱ ከጀነቶ በር - ሸህ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አልአሙዲ አደባባይ-ስታዲየም- እቴጌ መናፈሻ- ከአዳጎ አደባባይ- ጎንደር በር አድርጎ በፒያሳ እስከ ጉቦ በር የ16 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን መሆኑን ተናግረዋል።
በ117 ሚሊዮን ብር በጀት የሚገነባው ከአዳጎ አደባባይ - ሙጋድ እስከ ጎንደር በር አደባባይ ያለው የ1 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ያለውን የኮሪደር ልማት ዘንድሮ ለማጠናቀቅ ስራው እየተፋጠነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህ የኮሪደር ልማትም ለ200 ሰዎች አዲስ የስራ እድል የፈጠረላቸው መሆኑን ጠቁመው፤ መላው የከተማው ህዝብ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጠል መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ከወልዲያ ከተማ ነዋሪዎች መካከለ አቶ ፍስሃ አያሌው በሰጡት አስተያየት፤ ተወልደው ያደጉባት ጥንታዊት የወልዲያ ከተማ በኮሪደር ልማቱ ገጽታዋ እየተቀየረ መምጣቱን ገልጸዋል።
በከተማዋ ባለው ጠባብ መንገድ እሰከ ዛሬ ተሽከርካሪዎችና እግረኞች በመጋፋት ለአደጋ እየተገለጥን ነበር ያሉት ነዋሪው፤ አሁን ላይ እየተገነባ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ይሄን መሰረታዊ ችግር የሚፈታ መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የስራ እድል አግኝተንበት ቤተሰባችንን እየመራን ነው ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026