የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የፋርማሲዩቲካል ዘርፍ ከኢትዮጵያም አልፎ የአፍሪካን የገበያ ድርሻ ለማግኘት ያስችላል - ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር)

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ፋርማሲዩታካል ዘርፍ መሰማራት ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካን የገበያ ድርሻ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ገለጹ።

የኢትዮ ህንድ የፋርማሲዩቲካል የንግድና የቢዝነስ ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በፎረሙ ላይ ከ80 በላይ የህንድ መድኃኒት፣ የህክምና ግብዓትና ቁሳቁስ አምራች ድርጅቶች ተሳትፈዋል።


ኮሚሽነሩ በዚህ ጊዜ ኢትዮጵያ አብዛኛው የመድኃኒት ፍላጎቷን የምታሟላው ከወጪ በማስገባት እንደሆነ ገልጸው በ10 ዓመት ሀገራዊ የልማት እቅዱ ይህንን ፍላጎት በሀገር ውስጥ ምርት ለመተካት ግብ መደረጉን ጠቁመዋል።

ለዚህም የቂሊንጦ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ዘመናዊ መሰረተ ልማትን አካቶ መዘጋጀቱን በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ለሚሳተፉ ባለሀብቶች የተለያዩ የታክስ ነጻና ማበረታቻዎች መዘጋጀታቸውን አመልክተዋል።

የህንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ፋርማሲዩቲካል የኢንቨስትመንት መስክ ባሉ የመድኃኒት አቅርቦት የህክምና መገልገያ ቁሳቁሶች ምርት፣ የጤና መሰረተ ልማት ግንባታ እና ዲጂታል ሄልዝ ላይ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።


በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ሽሪ አኒል ኩማር ራይ ኢትዮጵያ ባለፉት 6 ዓመታት ለንግድና ለኢንቨስትመንት ምቹ የሆኑ የፖሊሲ ማሻሻያዎችን እየተገበረች እንደምትገኝም ገልጸዋል።

የህንድ ባለሀብቶችም ያለውን ምቹ ሁኔታ ተጠቅመው መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ለኩባንያዎቹ የኢትዮጵያ ፋርማሲዩቲካል ኢንቨስትመንት አማራጭን በተመለከተ ገለጻ እንደተደረገላቸው ከኮሚሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026