የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ዓለም አቀፍ የንግድ ትርኢቶች ከወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ተጨማሪ አቅም እየፈጠሩ ነው

Apr 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 28/2017(ኢዜአ):-በተለያዩ አገሮች የሚካሄዱ ዓለም አቀፍ የንግድ ትርኢቶች ምርትን ከማስተዋወቅ ባለፈ ከወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ ተጨማሪ አቅም እየፈጠሩ መሆኑተገለጸ።


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ እንደገለጹት፥መንግስት ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለዓለም ገበያ እንዲቀርብ በርካታ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል።


በዚህም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ለማስተዋወቅና የገበያ ተደራሽነታቸውን ለማስፋት በተለያዩ ዓለም አቀፍ ኩነቶች ላይ የሚደረገው ተሳትፎ መጨመሩን ተናግረዋል።


እ.ኤ.አ በ2025 በቻይና በተደረገው ሰባተኛው ዓለም አቀፍ የገቢ ምርቶች ፣በጃፓን ኦሳካ የቅባትና እና ጥራጥሬ ትርዔት እንዲሁም በዱባይ የንግድ ትርዔት ላይ የኢትዮጵያ ኩባንያዎች መሳተፋቸውን አስታውሰዋል።


የንግድ ትርኢቶቹ የኢትዮጵያን ምርት ከማስተዋወቅ በተጨማሪ አዳዲስ ስምምነቶችን በመፈጸም በዘርፉ የሚገኘው ገቢ እንዲያድግ ትልቅ አስተዋጾኦ እያበረከቱ መሆኑን ነው ያስረዱት።


ለአብነትም በዱባይ የንግድ ትርዒት የተሳተፉ 31 ኩባንያዎች በተለያዩ አገራት ከሚገኙ ኩባንያዎች ተጨማሪ የውል ስምምነት መፈራረማቸውን አንስተዋል፡፡


አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ላኪዎችን በማበረታታት እንዲሁም ቅድሚያ በመስጠት ለውጤታማነት አስቻይ ሁኔታዎችን መፍጠሩን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊው አስታውቀዋል።


በተለያዩ አገራት የሚከናወኑ ዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒቶች ከወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ እያሳደጉ በመሆኑ እንደ አገር የሚደረገው ተሳትፎ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።


በዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒቶት ተሳትፎ ካደረጉ የንግድ ድርጅቶች መካከል የማይክሮ ፋርማ ስራ አስኪያጅ አቶ ፋሲል ታረቀኝ በበኩላቸው፤ የማይክሮ ፋርማ የግብርና ምርቶችን በመያዝ በዓለም አቀፍ የንግድ ትርዒቶች እየተሳተፉ እንደሚገኝ ተናግረዋል።


በንግድ ትሪዒቶቹ ምርቶችን ከማስተዋወቅ በተጨማሪ ደንበኛን ከመፍጠር አኳያ ትልቅ ሚና መጫወቱን አስታውቀዋል፡፡


በቀጣይም እንዲህ ዓይነት ዝግጅቶች የኢትዮጵያን ምርት ይበልጥ ለማስተዋወቅ እና ተጨማሪ የገበያ መዳረሻዎችን ለመፍጠር ወሳኝ በመሆናቸው ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026