
አዲስ አበባ፤መጋቢት 29/2017 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 የአምራች ኢንዱስትሪዎች አውደርዕይን ከፍተዋል።
አውደ ርዕዩ "ከሸማችነት ወደ አምራችነት" በሚል መር ሃሳብ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሚያዝያ 4 ቀን 2017 በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ይካሄዳል።
በመርኃግብሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል፣የአዲስ አበባ ምክርቤት አፈጉባኤ ቡዜና አልከድር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ፣ በብልፅግና ፓርቲ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሞገስ ባልቻ እና ሌሎች የአስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ200 በላይ የተለያዩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን ያቀረቡበት ነው፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዚሁ ጊዜ እንደተናገሩት፤ አስተዳደሩ ቀዳሚ ትኩረት ከሰጣቸው ዘርፎች የአምራች ኢንዱስትሪ ዋነኛው ነው።
የዘርፉን ተግዳሮት በመፍታት ከተማዋን የኢንዱስትሪ ማዕከል ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በበኩላቸው፥ መንግስት የኢትዮጵያን ብልፅግና እውን ለማድረገ በትኩረት እየሰራ ነው ብለዋል።
በዚህ ሂደት የአምራች ኢንዱስትሪ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ በርካታ ተግባራት እየተከናወነ መሆኑንም አመላክተዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ጃንጥራር አባይ፥ ለአምራቾች መሰረት ልማቶችን በማሟላት፣ የፋይናንስና ማሽነሪ አቅርቦት በማሳደግ እንዲሁም ማስፋፊያ ቦታዎችን በማቅረብ ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026