የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮጵያና እስራኤል ያላቸውን የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር ይገባል - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር

Apr 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና እስራኤል በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።

አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በኡዝቤኪስታን እየተካሄደ ከሚገኘው 150ኛው የኢንተር ፓርላሜንታሪ ኅብረት/አይፒዩ/ መድረክ ጎን ለጎን በሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ከእስራኤል የፓርላማ ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል።


አቶ አገኘሁ ኢትዮጵያና እስራኤል ዘመናትን የተሻገረ መልካም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅሰው በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በቱሪዝም መስክ ያላቸውን ግንኙነት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በዘመናዊ ግብርና ዘርፎች ያለውን አሠራር አጠናክሮ መቀጠል እንደሚፈልግ ጠቅሰው በዘርፎቹ በትብብር መሥራት ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን በመግለፅም የእስራኤል ባለሃብቶች በልዩ ልዩ ዘርፎች ቢሰማሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።

የእስራኤል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ(Speaker of the Knesset) አሚን ኦሃና እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት በአኮኖሚና በዲፕሎማሲ ወደ ላቀ ደረጃ የማድረስ ፍላጎት አላት ብለዋል።

የሁለትዮሽ ትብብሩን ማጠናከር እንደሚገባና የህግ አውጪ ምክር ቤቶች ትስስር ማጎልበት ወሳኝ እንደሆነ መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.