
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና እስራኤል በንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር መስራት እንደሚገባ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።
አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በኡዝቤኪስታን እየተካሄደ ከሚገኘው 150ኛው የኢንተር ፓርላሜንታሪ ኅብረት/አይፒዩ/ መድረክ ጎን ለጎን በሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ከእስራኤል የፓርላማ ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል።

አቶ አገኘሁ ኢትዮጵያና እስራኤል ዘመናትን የተሻገረ መልካም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅሰው በንግድ፣ በኢንቨስትመንትና በቱሪዝም መስክ ያላቸውን ግንኙነት አጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂና በዘመናዊ ግብርና ዘርፎች ያለውን አሠራር አጠናክሮ መቀጠል እንደሚፈልግ ጠቅሰው በዘርፎቹ በትብብር መሥራት ሁለቱን ሀገራት ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርግም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት እያስመዘገበች መሆኑን በመግለፅም የእስራኤል ባለሃብቶች በልዩ ልዩ ዘርፎች ቢሰማሩ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።
የእስራኤል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ(Speaker of the Knesset) አሚን ኦሃና እስራኤል ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት በአኮኖሚና በዲፕሎማሲ ወደ ላቀ ደረጃ የማድረስ ፍላጎት አላት ብለዋል።
የሁለትዮሽ ትብብሩን ማጠናከር እንደሚገባና የህግ አውጪ ምክር ቤቶች ትስስር ማጎልበት ወሳኝ እንደሆነ መግለጻቸውን ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026