
ባህር ዳር፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በተለያዩ የስራ ዘርፎች ለተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ከ3 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የገበያ ትስስር መፈጠሩን የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ አስታወቀ።
በቢሮው የገበያ ልማት ባለሙያ አቶ መኳንንት እማኘ ለኢዜአ እንደገለፁት ለኢንተርፕራይዞቹ የገበያ ትሰስር መፍጠር የተቻለው በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ እድሎችን በመጠቀም ነው።
በዚህም ለ23ሺህ 119 ኢንተርፕራይዞች የገበያ ትስስር መፈጠሩን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ በውጭ ሀገራት ትስስር የተፈጠረላቸው 62 ኢንተርፕራይዞች 319ሺህ 609 የአሜሪካ ዶላር አስገኝተዋል ብለዋል።
ትስስሩን መፍጠር የተቻለውም በጨርቃጨርቅና አልባሳት፣ በእንጨትና ብረታ ብረት፣ በኮንስትራክሽን፣ በቆዳና ቆዳ ውጤቶች፣ በባህላዊ ጌጣጌጥና አልባሳት እንዲሁም በሌሎች የግብርና ውጤቶች መሆኑን ተናግረዋል።
በተጨማሪም በግብርናው ዘርፍ በእንስሳት ውጤቶችና ሌሎች የግብርና ምርቶች ትስስር መፍጠር መቻሉን አስረድተዋል።
በሀገር ውስጥ የተፈጠረው የገበያ ትስስር ከከፍተኛ አምራች ኢንዱስትሪዎች፣ ከዩኒቨርሲቲዎች፣ ከመንግስትና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶችና ሌሎች ተቋማት ጋር እርስ በርስ ጭምር መሆኑንም አመልክተዋል።
በደሴ ከተማ የቧንቧ ውሃ ክፍለ ከተማ ነዋሪ ወጣት ዳዊት ጌቱ በሰጠው አስተያየት ሶስት ሆነው በመደራጀት ያገለገሉ የፕላስቲክ ውጤቶችን ፈጭተው ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ ተጠቃሚ መሆናቸውን ተናግሯል።
መንግስት ባመቻቸላቸው ቦታና ከ700ሺህ ብር በላይ ብድር የፕላስቲክ መፍጫ ማሽን ገዝተው ወደ ስራ በመግባት በአዲስ አበባ ከተማና በሌሎች ክልሎች ምርታቸውን በማቅረብ ላይ መሆናቸውን አስረድቷል።
በዚህም በ350ሺህ ብር የጀመሩት ሥራ አሁን ላይ ካፒታላቸውን ሶስት ሚሊዮን ብር ማድረስ እንደቻሉም አስታውቀዋል፡፡
በ60ሺህ ብር የጀመሩት የጨርቃጨርቅና አልባሳት ስራ አሁን ላይ ካፒታላቸውን አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ማድረሳቸውን የገለጹት ደግሞ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪ ወይዘሮ ሶፊያ መሀመድ ናቸው።
በባዛሮችና በንግድ ትርዒቶች በሚፈጠርላቸው የገበያ ትስስር ምርታቸውን በማስተዋወቅና በመሸጥ ተጠቃሚ ከመሆናቸው ባሻገር ወጣቶችን በልብስ ስፌት በማሰልጠን ራሳቸውን እንዲችሉ እያገዙ መሆኑን ተናግረዋል።
በቀጣይም በውጭና በሀገር ውስጥ የገበያ ትስስር የማመቻቸቱ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመልክቷል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026