የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 359 ሺህ ሄክታር መሬት ይለማል - ቢሮው

Apr 9, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 359 ሺህ ሄክታር መሬት እንደሚለማ የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለፀ።

የ2017 ዓ/ም ክልላዊ የበልግ አዝመራ የበቆሎ ክላስተር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በጊምቦ ወረዳ ተካሂዷል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው እንደገለፁት በክልሉ የበልግ አዝመራ በሰፊው የሚከናወን ሲሆን በዘንድሮም 359 ሺህ ሄክታር ማሳ በተለያዩ ሰብሎች ይለማል።

በዚህም ዋና ዋና ሰብሎችን ጨምሮ ከ13 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልጸዋል።

የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግና ከሚለማው አጠቃላይ ማሳ ውስጥ 30 በመቶውን በክላስተር በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በዛሬው እለትም በጊምቦ ወረዳ ሾምባ ሼካ ቀበሌ ክልላዊ የኩታ ገጠም እርሻ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር መከናወኑን ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የቀበሌው አርሶ አደሮች የአፈር ማዳበሪያና ምርጥ ዘር አጠቃቀም ላይ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደነበረ ያነሱት አቶ ማስረሻ አሁን ላይ መሻሻል እንዳለ ገልፀዋል።

የክልሉ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማን በበኩላቸው፣ ለግብርናው ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት ከዚህ ቀደም ጦም ያደረ መሬት እንዲታረስ፣ ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲቀርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ በመስኖ የማልማት ልምዱ እንዲዳብር በተሰራ ስራም ውጤት እየመጣ መሆኑን ገልፀው ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

ከተለመደው አሰራር በመላቀቅ ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም፣ ማሳን መንከባከብና ምርትን በወቅቱ መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑንም ተናግረዋል።

የግብርና ባለሙያዎች አርሶ አደሩን በማንቃትና በማነቃቃት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም አቶ ፍቅሬ አሳስበዋል።

የካፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳሻው ከበደ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ በዞኑ የበልግ አዝመራ ውጤታማ እንዲሆን ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በዘንድሮ የበልግ አዝመራ 95ሺህ 951 ሄክታር መሬት በማልማት ከ4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ የዞኑ ግብርና፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ጋዎ አባመጫ ተናግረዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይም የክልል፣ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026