
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በናይጄሪያ የመከላከያ መረጃ ዋና ኃላፊ ፓርከር አንዳያዳይ የተመራ ወታደራዊ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ ላይም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታዬ ግርማ (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ አባላት ስለኢንስቲትዩቱ ስራዎች ገለፃ አድርገዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ “አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለሁሉም” በሚል መሪ ሐሳብ ከሚሠራቸው ሥራዎች በተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም እንዲያቋቁሙ መነሻ መሆን መቻሉን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

አፍሪካ ውስጥ በዘርፉ በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል አለመኖር አኅጉሪቱ በሚፈለገው ደረጃ ተጠቃሚ እንዳትሆን እንቅፋት መሆኑንም ገልጸዋል።
የናይጄሪያ ወታደራዊ ልዑካን ቡድን አባላት በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ከአህጉር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ግዙፍ ዳታ ሴንተር መገንባቱን እንዳደነቁ የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።

የሰው ሃብት ልማት ላይ እየሠራ ያለው ሥራም የሚያኮራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለአፍሪካ ሀገራት አርዓያ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026