የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በናይጄሪያ መከላከያ መረጃ ዋና ሃላፊ የተመራ ልኡክ የአርቲፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎበኘ 

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በናይጄሪያ የመከላከያ መረጃ ዋና ኃላፊ ፓርከር አንዳያዳይ የተመራ ወታደራዊ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።

በጉብኝቱ ላይም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታዬ ግርማ (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ አባላት ስለኢንስቲትዩቱ ስራዎች ገለፃ አድርገዋል፡፡

ኢንስቲትዩቱ “አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለሁሉም” በሚል መሪ ሐሳብ ከሚሠራቸው ሥራዎች በተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም እንዲያቋቁሙ መነሻ መሆን መቻሉን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡


አፍሪካ ውስጥ በዘርፉ በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል አለመኖር አኅጉሪቱ በሚፈለገው ደረጃ ተጠቃሚ እንዳትሆን እንቅፋት መሆኑንም ገልጸዋል።

የናይጄሪያ ወታደራዊ ልዑካን ቡድን አባላት በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ከአህጉር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ግዙፍ ዳታ ሴንተር መገንባቱን እንዳደነቁ የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።


የሰው ሃብት ልማት ላይ እየሠራ ያለው ሥራም የሚያኮራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለአፍሪካ ሀገራት አርዓያ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026