
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በናይጄሪያ የመከላከያ መረጃ ዋና ኃላፊ ፓርከር አንዳያዳይ የተመራ ወታደራዊ ልዑክ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን ጎብኝቷል።
በጉብኝቱ ላይም የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ታዬ ግርማ (ዶ/ር) ለልዑካን ቡድኑ አባላት ስለኢንስቲትዩቱ ስራዎች ገለፃ አድርገዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ “አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለሁሉም” በሚል መሪ ሐሳብ ከሚሠራቸው ሥራዎች በተጨማሪ የአፍሪካ ሀገራት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም እንዲያቋቁሙ መነሻ መሆን መቻሉን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

አፍሪካ ውስጥ በዘርፉ በቂ የሰለጠነ የሰው ኃይል አለመኖር አኅጉሪቱ በሚፈለገው ደረጃ ተጠቃሚ እንዳትሆን እንቅፋት መሆኑንም ገልጸዋል።
የናይጄሪያ ወታደራዊ ልዑካን ቡድን አባላት በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ ከአህጉር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ግዙፍ ዳታ ሴንተር መገንባቱን እንዳደነቁ የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያመለክታል።

የሰው ሃብት ልማት ላይ እየሠራ ያለው ሥራም የሚያኮራ መሆኑን ገልጸው፤ ይህም ለአፍሪካ ሀገራት አርዓያ ያደርገዋል ብለዋል፡፡
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026