መቀሌ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል በውሃ ዕቀባ እና የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን የማሳደግ ስራ በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ ገለጸ።
በክልሉ በዘንድሮው መኸር በሄክታር በአማካይ 21 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ አበራ ከደነው ለኢዜአ እንደተናገሩት የውሃ ዕቀባ ስራዎችን በማከናወን የዝናብ እጥረት ችግርን ከመከላከል ባሻገር የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በውሃ ዕቀባ ስራው አብዛኞቹ የክልሉ አርሶ አደሮች የሚሳተፉ ሲሆን እርጥበትን የማቀብ ዘመቻውም እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2017 ዓ/ም እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የእርሻ ፓኬጅ ዝግጅትና አጠቃቀም እንዲሁም የማስፈፀም አቅምን ማጎልበት የሚያስችል ስልጠና ለሁሉም ባለሙያዎች እና አርሶ አደሮች በመስጠት ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በመኸር ወቅት ከአንድ ሄክታር መሬት በአማካይ 21 ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ የእርሻ ዝግጅት እና ግብዓት አቅርቦት እየተሟላ መሆኑን ገልጸዋል።
በመሆኑም የተፈጥሮና የሰው ሰራሽ የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር እንዲሁም የእርሻ ትራክተሮች ከወዲሁ ለአርሶ አደሩ እንዲደርሱ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ከፌደራል መንግስት ወደ ክልሉ እስካሁን የተጓጓዘውን ከ150 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ወረዳዎች የማዳረስ ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በመኸር ወቅት 16 ሚሊዮን ኩንታል የተፈጥሮ ማዳበሪያና ኮምፖስት ጥቅም ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።
በ2017/18 የምርት ዘመን በክልሉ 758ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 16 ሚሊዮን ኩንታል ለመሰብሰብ ታቅዷል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025