
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፡- የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ እንደሀገር ለተጀመረው የክህሎት ልማት መስፈንጠሪያ እንደሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
በሰመር ካምፕ እና በክህሎት ኢትዮጵያ መርኃ ግብር የተሰሩ የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ ትናንት ተከፍቷል።

ባንኩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርቀው ከፍተውታል።
ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ በባንኩ የሚገኙት የፈጠራ ውጤቶች በባለፈው ዓመት የሰመር ካምፕ ፕሮግራም እንዲሁም በዘንድሮ የክህሎት ኢትዮጵያ ተሳታፊዎች የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሚገኝበት ነው።
የክህሎት ባንክ የቴክኖሎጂ ባለቤቶችን የፈጠራ ምርቶችን መጠቀምና ማስመረት ከሚፈልጉ ደንበኞች ጋር የሚያገናኝ መሆኑን ገልጸዋል።
ባንኩ ለጎብኚዎች ክፍት ሲሆን የመንግስት እና የግል ዘርፉ የፈጠራ ውጤቶችን በመጎብኘት እንዲመረትላቸው የሚፈልጓቸውን የቴክኖሎጂ ምርትች ትዕዛዝ መስጠት የሚችሉበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ተናግረዋል።
ይህ ለሀገሪቱ የመጀመሪያው የሆነው የክህሎት ባንክ ለክህሎት ልማት ትልቅ መስፈንጠሪያ እንደሚሆንም ነው ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የገለጹት።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ21 ኢንተርፕራይዞች ያዘጋጀው የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተደርጓል።

የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ርክክብ የተደረገው የፈጠራ ሀሳብን ወደ ተግባር ለቀየሩ ስራ ፈጣሪዎች ነው ብለዋል።

የማሽነሪና በቀላሉ ድጋፍ አግኝተው ወደ ገበያ መውጣት ለሚችሉ የስራ ፈጠራዎች ርክከብ መደረጉን ነው የገለፁት።

የቦታ ርክክብ የተደረገላቸው የፈጠራ ባለቤቶች የሆኑት እሱባለሁ አለልኝ እና አህላም አሊ ድጋፉ የፈጠራ ስራቸውን በስፋት ለመስራት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026