የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በሰሜን ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ከለማው የስንዴ ሰብል የደረሰው እየተሰበሰበ ነው

Apr 14, 2025

IDOPRESS

ወልዲያ ፤ ሚያዝያ 4/2017(ኢዜአ)፡- በሰሜን ወሎ ዞን በዘንድሮ የበጋ ወቅት በ20 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ከለማው የስንዴ ሰብል ውስጥ የደረሰው እየተሰበሰበ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

እስካሁንም በአምስት ሺህ 625 ሄክታር መሬት ላይ የደረሰ የስንዴ ሰብል መሰብሰቡን መምሪያው ገልጿል።

በመምሪያው የአትክልት፣ ፍራፍሬና መስኖ ቡድን መሪ አቶ አለባቸው መራዊ፤ በመስኖ እየለማ ያለው የበጋ ስንዴ ልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳዳገው እንደሚገኝ ለኢዜአ ተናግራል።

በዚህም በዘንድሮው የበጋ ወቅት በተካሄደው የመስኖ ልማት ከተሸፈነው 20 ሺህ ሄክታር መሬት የስንዴ ሰብል ላይ ከ728 ሺህ ኩንታል በላይ ምርትም እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረትም በአምስት ሺህ 625 ሄክታር የተዘራውን ሰብል በመሰብሰብ 212 ሺህ ኩንታል ምርት ማምረት መቻሉን አስታውቀዋል።


በበጋ ስንዴ ልማቱ እየተካሄደ የሚገኘውም 45 ሺህ 542 አርሶ አደሮች በማሳተፍ እንደሆነ ጠቀሰው፤ የምርት አሰባሰቡ እስከ ሚያዝያ ወር አጋማሽ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

የሰንዴ ምርት በማይታወቅባቸው ቆላማ አካባቢዎች አሁን ላይ ከፍተኛ የስንዴ ምርት እየተገኘ መሆኑን ጠቁመው፤ ምርታማነቱም በሄክታር እስከ 45 ኩንታል መድረሱን አብራርተዋል።

የስንዴ ልማቱ ከውጭ የሚገባውን ከመተካት ባሻገር የምግብ ሉአላዊነትን ለማረጋገጥ የተያዘውን ግብ ለማሳካት አጋዥ ሚና እንዲጫወት ዞኑ የበኩሉን እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።


ከሃብሩ ወረዳ አርሶ አደሮች ውስጥ አብዱ አራጋው በሰጡት አስተያየት፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በስንዴ ልማት በመሰማራታቸው ምርታማነታቸውን ማሳደግ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል።

በዘንድሮ በጋም መስኖን በመጠቀም ከግማሽ ሄክታር በላይ ማሳቸውን በስንዴ በማልማት አሁን ላይ ሰብሉን ሰብስበው በመውቃት 19 ኩንታል ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

የስንዴ ምርት በአካባቢ ገበያም ሆነ በምግብ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች ተፈላጊነቱ ከፍተኛ በመሆኑ የልፋታችንን ዋጋ የሚከፍል አዋጭ ምርት ነው ብለዋል።

በዚሁ ወረዳ የቄስ ቀበሌ አርሶ አደር ሃይሉ ዳምጤ፤ ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በመስኖ ያለሙት የበጋ ስንዴ አሁን ላይ እየታጨደ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

የሰንዴ ሰብሉን ያለሙት በሩብ ሄክታር መሬታቸው ላይ እንደሆነም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026