
መቀሌ፤፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ዜጎችን በስራ በማሳተፍ ተጠቃሚ የሚሆኑበትና ለሶስት ዓመታት የሚቆይ ሁለተኛው ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ዛሬ በመቀሌ ከተማ መጀመሩ ተገለፀ።
የፌዴራል መንግስት በመደበው ከ670 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ወደ ተግባር የገባው ፕሮግራሙ በተለያዩ የከተማ ጽዳትና ውበት ስራዎች ላይ የሚሳተፉ 3ሺህ 447 የቤተሰብ መሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግም ተገልጿል።
የፕሮግራሙ መጀመርን አስመልክተው የመቀሌ ከተማ የሴፍቲኔት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ተሻለ ብርሃነ እንዳሉት፤ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች እያዳንዳቸው ቢያንስ አራት ቤተሰቦችን የሚያስተዳድሩ ናቸው።

የሁለተኛው ዙር የሴፍቲኔት ፕሮግራም ዓላማም ተጠቃሚዎችን ለሶስት ዓመታት በተለያዩ ስራዎች ላይ በማሳተፍ ዘላቂ የገቢ ምንጭ ወደሚያገኙበት የስራ ሁኔታ እንዲሸጋገሩ ማድረግ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመጀመሪያው ዙር የሴፍትኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ የነበሩ 3ሺህ 215 የቤተሰብ መሪዎች በቀጣዩ ወር እንደሚመረቁ አስተባባሪው ገልጸዋል።
የፌዴራል መንግስት ለመጀመሪያውና ሁለተኛው ዙር ፕሮግራም ማስፈጸሚያ ከ670 ሚሊዮን ብር በላይ መመደቡን አስረድተዋል።
በፕሮግራሙ ተሳታፊ ከሆኑ የቤተሰብ መሪዎች መካከል ወይዘሮ አዝመሩ ካሳ እንዳሉት እስከ አሁን በቀን ስራ እየተንቀሳቀሱ ቤተሰባቸውን ሲያስተዳድሩ ቆይተዋል።
ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚሳተፉበት የሴፍቲኔት ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸው ወደ ተሻለ ህይወት ለመሸጋገር እንደመደላድል እንደሚጠቅማቸው ተናግረዋል።
ሰርቶ በመለወጥ ወደ ተሻለ ስራ ለመሸጋገር የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ስራው መልካም አጋጣሚ መሆኑን የተናገረው ደግሞ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣት ተክላይ ሀይላይ ነው።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026