የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ኢትዮ ኮደርስ ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂን በማስታጠቅ የአሰራር ስርዓትን ያዘምናል - ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ሚያዚያ 7/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮ ኮደርስ ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጂን በማስታጠቅ የአሰራር ስርአትን የሚያዘምን በመሆኑ ለስኬታማነቱ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አስገነዘቡ።

ክልል አቀፍ የኢትዮ-ኮደርስ ኢንሼቲቭ አፈጻጸም ግምገማና የንቅናቄ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ ተካሂዷል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ በወቅቱ እንዳሉት ዲጂታል ማህበረሰብን መፍጠር የብልጽግና ጉዞን ለማሳካት ትልቅ መሣሪያ በመሆኑ የኢትዮ-ኮደርስ ፕሮጀክትም ለስኬቱ አጋዥ ነው።

ይህን እውን ለማድረግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደር መዋቅሮች ብቃት ያለው አመራር መስጠት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

ኢትዮ ኮደርስ ስልጠናም ዘመኑን የዋጀ የፐብሊክ ሰርቪስ አገልግሎትን በመዘርጋት የአሰራር ስርዓትን ለማዘመን ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።


አገልግሎቱን ትልቅ መሠረተ ልማትን መገንባት ሳያስፈልግ በእጅ ባሉ ስልኮችና ኮምፒውተሮች ብቻ የዲጂታል እውቀትን በማዳበር ማህበረሰብን ማገልገል የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የክልሉ ሳይንስ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ ተካልኝ ጋሎ በበኩላቸው ኢትዮ ኮደርስ ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የማይተካ ሚና ስላለው ቢሮው ይህን ለመተግበር እየሰራ ነው ብለዋል።

ወጣቱን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና የሥራ ባለቤት እንዲሆንና ሁለንተናዊ ሀገራዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ መሆኑንም ገልፀዋል።

ለተግባራዊነቱም ክልሉ በሶስት ዓመታት ከ235ሺህ በላይ ዜጎችን ተሳታፊ ለማድረግ በየዓመቱ ከ58ሺህ በላይ ዜጎችን የዕድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ ጥረት እያደረገ እንደሆነም ጠቅሰዋል።


ዲጂታል ቴክኖሎጂ የሰውን ልጅ ህይወትና አኗኗር ከማቅለልና ዲጂታል ማህበረሰብን ከመፍጠር አኳያ ድርሻው ጉልህ መሆኑን የጠቀሱት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት አብደላ ከማል(ዶ/ር) ናቸው።

ያለ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የአንድ ሀገር ዕድገት ሊረጋገጥ የማይችል በመሆኑ ዩኒቨርሲቲው የኢትዮ-ኮደርስ ፕሮጀክት ዕቅድ እንዲሳካ የበኩሉን እንደሚወጣም አረጋግጠዋል።

ለአንድ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፕሬዚዳንቶች፣ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ዲኖች፣ የዞን ዋና አስተዳዳሪዎች፣ የመንግስት ተጠሪዎች፣ ከንቲባዎችና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026