
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 15/2017 (ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማን ሥምና ዝና ለመመለስ እየተከናወነ ላለው የመልሶ ግንባታ ልማት "ኑ ጎንደርን እንሞሽር" በሚል መሪ ሀሳብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ሊካሄድ መሆኑን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።
የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ቻላቸው ዳኛው በሰጡት መግለጫ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማን የቀደመ ስምና ዝና ለመመለስ የመልሶ ግንባታ እና መሰረተ ልማትን የማሟላት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የከተማዋን መልሶ ግንባታ በማስጀመር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባቸው የነበሩ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲታደሱ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ለዓመታት ደብዝዞ የቆየው የጎንደር ገጽታ መፍካቱን ነው የጠቀሱት።
የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ኢትዮጵያውያን የድርሻቸውን እንዲወጡ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጥሪ አቅርበዋል።
የጎንደርን የትንሳኤ ጉዞ ማሳካት አለብን ያሉት አቶ ቻላቸው፥ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ጎንደርን በማልማት ስራ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ያለመ መሆኑንም አንስተዋል።
በመሆኑም በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚገኙ የጎንደር ተወላጆች፣ መላው ኢትዮጵያውያን፣ የዓለምአቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026