
አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 15/2017 (ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማን ሥምና ዝና ለመመለስ እየተከናወነ ላለው የመልሶ ግንባታ ልማት "ኑ ጎንደርን እንሞሽር" በሚል መሪ ሀሳብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ሊካሄድ መሆኑን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።
የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ቻላቸው ዳኛው በሰጡት መግለጫ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል እንደሚካሄድ ተናግረዋል።
የጎንደር ከተማን የቀደመ ስምና ዝና ለመመለስ የመልሶ ግንባታ እና መሰረተ ልማትን የማሟላት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የከተማዋን መልሶ ግንባታ በማስጀመር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባቸው የነበሩ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲታደሱ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
በዚህም ለዓመታት ደብዝዞ የቆየው የጎንደር ገጽታ መፍካቱን ነው የጠቀሱት።
የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ኢትዮጵያውያን የድርሻቸውን እንዲወጡ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጥሪ አቅርበዋል።
የጎንደርን የትንሳኤ ጉዞ ማሳካት አለብን ያሉት አቶ ቻላቸው፥ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ጎንደርን በማልማት ስራ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ያለመ መሆኑንም አንስተዋል።
በመሆኑም በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚገኙ የጎንደር ተወላጆች፣ መላው ኢትዮጵያውያን፣ የዓለምአቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026