
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ):-በሐረሪ ክልል ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በትኩረት ይሰራል ሲሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የማህበራዊ ልማት ዘርፍ የሰው ሀብት ልማት እና መልካም አስተዳደር ዘርፍ ክንውኖችን ገምግሟል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በግምገማው ወቅት እንደገለፁት፥ በክልሉ ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
በተለይ የትምህርት እና ጤናው ዘርፍ ጤናማ፤ብቁ፤ክህሎት ያለው እና አምራች ዜጋን ማፍራት ቁልፍ ስራቸው አድርገው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
በጤናው ዘርፈው በሽታን መከላከል ብሎም አክሞ ማዳንን መሰረት ያደረገ ስራ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል በትምህርት ዘርፍ ሐረር በ12ኛ ክፍል የማሳለፍ ምጣኔ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
በተለይ ባለፈው ዓመት ሁሉም የከተማ እና ገጠር ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲ ማሳለፍ ችለዋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተመዘገበውን ውጤት ማስፋት ይገባል ብለዋል።
የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥን ማስቀረት እና የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ እንደሚገባም አክለዋል።
በሌላ በኩል የክልሉ ህዝብ የጋራ ባህል፤ታሪክ እና ማንነት ያለው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አብሮነት እና ወንድማማችነትን ይበልጥ የሚያጎለብቱ የወል ትርክትን የሚያሰርፁ ተግባራትን በትኩረት ማከናወን ይገባል።
በተለይ ወቅቱን የዋጀ የባህል ልማት ስራ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ብቁ፤ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር ልዩነት የሌለበት፤ፍትሀዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የተጀመረውን ውጤት ማስፋት እንደሚገባ ገልፀዋል።
አመራሩም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ቁልፍ ስራው አድርጎ በመውሰድ ከማህበረሰቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን በዕቅድ ይዞ መፍታት ይጠበቅበታል መባሉን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026