
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ):-በሐረሪ ክልል ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ በትኩረት ይሰራል ሲሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የማህበራዊ ልማት ዘርፍ የሰው ሀብት ልማት እና መልካም አስተዳደር ዘርፍ ክንውኖችን ገምግሟል።
ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ በግምገማው ወቅት እንደገለፁት፥ በክልሉ ማህበራዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ።
በተለይ የትምህርት እና ጤናው ዘርፍ ጤናማ፤ብቁ፤ክህሎት ያለው እና አምራች ዜጋን ማፍራት ቁልፍ ስራቸው አድርገው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
በጤናው ዘርፈው በሽታን መከላከል ብሎም አክሞ ማዳንን መሰረት ያደረገ ስራ መስራት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በሌላ በኩል በትምህርት ዘርፍ ሐረር በ12ኛ ክፍል የማሳለፍ ምጣኔ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።
በተለይ ባለፈው ዓመት ሁሉም የከተማ እና ገጠር ትምህርት ቤቶች ተማሪዎችን ወደ ዩኒቨርሲቲ ማሳለፍ ችለዋል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የተመዘገበውን ውጤት ማስፋት ይገባል ብለዋል።
የተማሪዎች መጠነ ማቋረጥን ማስቀረት እና የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ እንደሚገባም አክለዋል።
በሌላ በኩል የክልሉ ህዝብ የጋራ ባህል፤ታሪክ እና ማንነት ያለው ነው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ አብሮነት እና ወንድማማችነትን ይበልጥ የሚያጎለብቱ የወል ትርክትን የሚያሰርፁ ተግባራትን በትኩረት ማከናወን ይገባል።
በተለይ ወቅቱን የዋጀ የባህል ልማት ስራ መስራት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ ብቁ፤ነፃና ገለልተኛ የሲቪል ሰርቪስ በመፍጠር ልዩነት የሌለበት፤ፍትሀዊ እና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የተጀመረውን ውጤት ማስፋት እንደሚገባ ገልፀዋል።
አመራሩም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት ቁልፍ ስራው አድርጎ በመውሰድ ከማህበረሰቡ የሚነሱ ቅሬታዎችን በዕቅድ ይዞ መፍታት ይጠበቅበታል መባሉን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026