
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የቡና ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሸበዲኖ ወረዳ ፉራ ቀበሌ ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ እንደገለጹት፤ በክልሉ ከ29 ሚሊዮን በላይ የተሻሻለ የቡና ችግኝ ለመትከል ታቅዷል።
ሙሉ ፓኬጅን በመጠቀም ወደ ተከላ የተገባው በክልሉ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል።

በባህር ዛፍ የተያዘ ሰፊ መሬትን ነጻ በማድረግ የቡና ልማት ላይ እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል።
ይህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
በዚህም ከባህር ዛፍ ነጻ የተደረገን ጨምሮ ከ11ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ተከላ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026