
ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የቡና ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሸበዲኖ ወረዳ ፉራ ቀበሌ ተጀምሯል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ እንደገለጹት፤ በክልሉ ከ29 ሚሊዮን በላይ የተሻሻለ የቡና ችግኝ ለመትከል ታቅዷል።
ሙሉ ፓኬጅን በመጠቀም ወደ ተከላ የተገባው በክልሉ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል።

በባህር ዛፍ የተያዘ ሰፊ መሬትን ነጻ በማድረግ የቡና ልማት ላይ እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል።
ይህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
በዚህም ከባህር ዛፍ ነጻ የተደረገን ጨምሮ ከ11ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ተከላ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026