የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ የቴክኖሎጂ ዘርፉን ለስራ እድል ፈጠራ በማዋል የዜጎችን ህይወት ለመለወጥ ጥረት እየተደረገ ነው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ ፤ሚያዚያ 17/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የቴክኖሎጂ ዘርፉን ለስራ እድል ፈጠራ በማዋል የዜጎችን ህይወት ለመለወጥ ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

በሲዳማ ክልል የቴክኖሎጂ፣ ክህሎትና የጥናትና ምርምር አውደ ርዕይ በሀዋሳ ሚሊኒየም አደባባይ ተከፍቷል።

የሲዳማ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ በየነ በራሳ፤ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ዘርፉን በማጠናከር ልማትን ለማፋጠን ግብ ተቀምጦ እየተተገበረ ነው ብለዋል።


በእስካሁኑ ሂደትም በክልሉ በመፍጠርና በማሻሻል እንዲሁም መቅዳትና ማሸጋገር የቻሉ በርካታ ተወዳዳሪ ዜጎች መፈጠራቸውን ጠቁመዋል።

ውጤቱንም ይበልጥ ለማሳደግ በዘርፉ ተሰማርተው ለሚንቀሳቀሱ አካላት ድጋፍ እንደሚያደርግላቸውም አቶ በየነ ተናግረዋል።

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ተወካይና የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት ለቴክኒክና ሙያ ዘርፎች በሰጠው ትኩረት ውጤት እየተመዘገበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ይህንንም ለማጠናከር ሙያንና ክህሎት ለማሳደግና ልምድ ለመለዋወጥ የሚያግዙ ውድድሮችና አውደ ራዕዮች እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቁመዋል።

የሲዳማ ክልል ስራ ክህሎትና ኢንተርፕራይዝ ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሀገረጽዮን አበበ በበኩላቸው በክልሉ በፈጠራና ቴክኖሎጂ ዘርፉ ያለውን ዕምቅ አቅም ለስራ ፈጠራና የዜጎች ህይወት የሚለውጥ እንዲሆን ታቅዶ በመሰራቱ ውጤት እየተመዘገበ ነው ብለዋል።

በተለይም ወደ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጆች ለመቀላቀል የነበረው አመለካከት በመቀየሩ በርካቶች በዚህ ሂደት እያለፉ ህይወታቸውን እየቀየሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በክልሉ ከራሳቸው አልፈው ሀገርን በዓለም አቀፍ ደረጃ መወከል የቻሉ ሰልጣኞች መፈጠራቸውን አንስተው ''ይህን አጠናክረን መቀጠል ይገባናል'' ብለዋል።

ለአራት ቀናት በሚቆየው በዚሁ ውድድር በክልሉ ከሚገኙ ከመንግስት፣ከግል ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የተውጣጡ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች እንዲሁም በኢንተርፕራይዞች የተሰሩ የፈጠራ ስራዎች መቅረባቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026