የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በህዳሴ ግድብ ግንባታ የታየውን የልማት ቁርጠኝነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት በሌሎችም መስኮች ማስቀጠል ይገባል

May 7, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ በህዳሴ ግድብ ግንባታ የታየውን የልማት ቁርጠኝነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት በሌሎችም መስኮች ማስቀጠል ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) ገለጹ።

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቅርተ ታምር የግድቡን አሁናዊ ሁኔታና የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀምን በተመለከተ ከጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል።


በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) እንዳሉት በግድቡ ግንባታ የታየውን ብሔራዊ አንድነት በሌሎች የልማት መስኮች በመድገም የሀገርን እድገት ማፋጠን ይገባል።

የህዳሴ ግድብ ግንባታ ወደ መጠናቀቅ ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸው፤ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የክልሉ ህዝብና መንግስት ሲያደርግ የቆየውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቅርተ ታምር በበኩላቸው የግድቡ ግንባታ የኢትዮጵያውያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ታሪካዊ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።


እንደ ሀገር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለግድቡ ግንባታ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን ገልጸው የግድቡ ግንባታ ቀሪ ስራ እስኪጠናቀቅ ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።

የጋምቤላ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ሃላፊ ኮማንደር ጋትቤል ቦል በበኩላቸው በክልሉ በበጀት ዓመቱ ለግድቡ ግንባታ 10 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ ሲሰራ መቆየቱን አመልክተዋል።

እቅዱን ለማሳካትም በቀሪ የበጀት ዓመቱ ወራት ጊዜ ውስጥ ያልተቋረጠ ርብርብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

በውይይቱ መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026