
ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ በህዳሴ ግድብ ግንባታ የታየውን የልማት ቁርጠኝነትና ህብረ ብሄራዊ አንድነት በሌሎችም መስኮች ማስቀጠል ይገባል ሲሉ የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) ገለጹ።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቅርተ ታምር የግድቡን አሁናዊ ሁኔታና የበጀት ዓመቱን የዘጠኝ ወራት አፈፃፀምን በተመለከተ ከጋምቤላ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አካሂደዋል።

በመድረኩ የተገኙት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) እንዳሉት በግድቡ ግንባታ የታየውን ብሔራዊ አንድነት በሌሎች የልማት መስኮች በመድገም የሀገርን እድገት ማፋጠን ይገባል።
የህዳሴ ግድብ ግንባታ ወደ መጠናቀቅ ምዕራፍ እየተቃረበ መሆኑን ገልጸው፤ ለፕሮጀክቱ ግንባታ የክልሉ ህዝብና መንግስት ሲያደርግ የቆየውን ሁለንተናዊ ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍቅርተ ታምር በበኩላቸው የግድቡ ግንባታ የኢትዮጵያውያንን አንድነት በተግባር ያሳየ ታሪካዊ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

እንደ ሀገር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለግድቡ ግንባታ ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ድጋፍ መሰብሰቡን ገልጸው የግድቡ ግንባታ ቀሪ ስራ እስኪጠናቀቅ ድጋፉ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
የጋምቤላ ክልል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ሃላፊ ኮማንደር ጋትቤል ቦል በበኩላቸው በክልሉ በበጀት ዓመቱ ለግድቡ ግንባታ 10 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ ታቅዶ ሲሰራ መቆየቱን አመልክተዋል።
እቅዱን ለማሳካትም በቀሪ የበጀት ዓመቱ ወራት ጊዜ ውስጥ ያልተቋረጠ ርብርብ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።
በውይይቱ መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026