
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሌ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የማዕድን ሃብትን በአግባቡ በማጥናትና በማልማት ከዘርፉ የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት እየተሰራ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን ማዕድን ልማት ለመሰማራት 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ጥያቄ ላቀረቡ 4ሺህ 326 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል።
በከፍተኛ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ የኮንስትራክሽን ዘርፍና በባህላዊ ማዕድን ምርት ለተሰማሩ ባለሃብቶች ፍቃዱ መሰጠቱን ነው የተናገሩት።
ቢሮው በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በካርታ የተደገፈ የማዕድን ክምችትና ልየታ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች እያካሄደ መሆኑንም አመልክተዋል።
የማዕድን ክምችት፣ አይነትና መጠንን ከመለየት ባለፈ የተገኙ ማዕድናትን በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን በመሳብ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዘጠኝ ወራት በተከናወኑ የማዕድን ፍለጋና ግመታ ጥናቶች ከታቀደው 80 በመቶ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።
በጥናቱ የኮንስትራክሽን፣ የኢንዱስትሪ፣ የኢነርጂ፣ ብረት ነክ እንዲሁም የከበሩና በከፊል የከበሩ ማዕድናትን በመለየት ለማዕድን ኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ቢሮ ሀላፊው አስታውቀዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026