የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ በማዕድን ዘርፍ 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሃብቶች ፈቃድ ተሰጥቷል - ቢሮው

May 8, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሌ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የማዕድን ሃብትን በአግባቡ በማጥናትና በማልማት ከዘርፉ የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት እየተሰራ ነው።

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን ማዕድን ልማት ለመሰማራት 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ጥያቄ ላቀረቡ 4ሺህ 326 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል።

በከፍተኛ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ የኮንስትራክሽን ዘርፍና በባህላዊ ማዕድን ምርት ለተሰማሩ ባለሃብቶች ፍቃዱ መሰጠቱን ነው የተናገሩት።

ቢሮው በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በካርታ የተደገፈ የማዕድን ክምችትና ልየታ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች እያካሄደ መሆኑንም አመልክተዋል።

የማዕድን ክምችት፣ አይነትና መጠንን ከመለየት ባለፈ የተገኙ ማዕድናትን በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን በመሳብ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

በዘጠኝ ወራት በተከናወኑ የማዕድን ፍለጋና ግመታ ጥናቶች ከታቀደው 80 በመቶ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።

በጥናቱ የኮንስትራክሽን፣ የኢንዱስትሪ፣ የኢነርጂ፣ ብረት ነክ እንዲሁም የከበሩና በከፊል የከበሩ ማዕድናትን በመለየት ለማዕድን ኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ቢሮ ሀላፊው አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026