
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሌ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የማዕድን ሃብትን በአግባቡ በማጥናትና በማልማት ከዘርፉ የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት እየተሰራ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን ማዕድን ልማት ለመሰማራት 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ጥያቄ ላቀረቡ 4ሺህ 326 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል።
በከፍተኛ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ የኮንስትራክሽን ዘርፍና በባህላዊ ማዕድን ምርት ለተሰማሩ ባለሃብቶች ፍቃዱ መሰጠቱን ነው የተናገሩት።
ቢሮው በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በካርታ የተደገፈ የማዕድን ክምችትና ልየታ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች እያካሄደ መሆኑንም አመልክተዋል።
የማዕድን ክምችት፣ አይነትና መጠንን ከመለየት ባለፈ የተገኙ ማዕድናትን በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን በመሳብ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዘጠኝ ወራት በተከናወኑ የማዕድን ፍለጋና ግመታ ጥናቶች ከታቀደው 80 በመቶ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።
በጥናቱ የኮንስትራክሽን፣ የኢንዱስትሪ፣ የኢነርጂ፣ ብረት ነክ እንዲሁም የከበሩና በከፊል የከበሩ ማዕድናትን በመለየት ለማዕድን ኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ቢሮ ሀላፊው አስታውቀዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026