
ሐረር፤ግንቦት 2/ 2017 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር የወተት፣ የዶሮ፣ የማርና የአሳ ምርታማነትን የማጎልበት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር አመለከቱ።
በክልሉ በሌማት ትሩፋት የእንስሳት ሀብት ልማትና ተዋጽኦዎችን ማጎልበት በሚቻልበት ዙሪያ በዘርፉ ከተሰማሩ አካላት ጋር ውይይት ተደርጓል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ሃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር በወቅቱ እንዳሉት፥በሌማት ትሩፋት የወተት፣የዶሮ፣የማርና የአሳ ምርታማነትን የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
በተለይ በአሁኑ ወቅት በክልሉ በከተማና በገጠር አርሶ አደሩን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በዶሮ፣በወተት ላም እርባታና የንብ ማነብ እንዲሁም በጓሮ አትክልት ልማት ላይ በመሳተፍ ምርትና ምርታማነት እንዲጎለብት እያስቻለ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ በሌማት ትሩፋት የሚመረቱ ምርቶችን ለገበያ በማቅረብ ህብረተሰቡ ዶሮ፣ ወተት፣እንቁላልና ሌሎች የእንስሳት ተዋጾዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ እና የገበያ ዋጋም እንዲረጋጋ ምቹ ሁኔታ እየተፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።
መድረኩም በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር የወተት፣የዶሮ፣ የማርና የአሳ ምርታማነትን ላይ የተጀመሩ ስራዎችን በተቀናጀ መልኩ ይበልጥ ለማጎልበት የሚያስችል በመሆኑ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።
ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል በዶሮ እርባታ ስራ የተሰማሩት አቶ እስክንድር ደግፌ፤ የክልሉ መንግስት በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የሚያደርገው የድጋፍ ስራዎች ውጤታማ እንዳደረጋቸው ጠቁመው በቀጣይም የመስሪያ ቦታ ችግር እንዲቀረፍላቸው ጠይቀዋል።
ሌላው በከብት እርባታ የተሰማሩት አቶ ከፍያለው ወርቁ፥ ከከብት መኖ ጋር በተያያዘ የሚታዩት ችግሮች እንዲቀረፉላቸው ጠይቀዋል።
የክልሉ ግብርና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ ነስረዲን አህመድ፤ ከሌማት ትሩፋት ስራዎች ጋር በተያያዘ ከመስሪያ ቦታ፣ ከከብት መኖ አቅርቦትና ሌሎች ችግሮች ምላሽ እንዲያገኙ የማድረግ ስራ እንደሚከናወን አመልክተዋል።
በመድረኩ ላይ በከተማው በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በወተት፣ ዶሮ፣ በማርና አሳ ሃብት ልማት ላይ የሚሰሩ አካላት ተሳትፈዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026