
ሆሳዕና፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በመጠናከራቸው በወቅቶች ሳንገደብ በመስራትና በማምረት ተጠቃሚ ሆነናል ሲሉ የሀዲያና የምስራቅ ጉራጌ ዞኖች አርሶ አደሮች ተናገሩ።
በዞኖቹ 545 ሄክታር መሬት ማልማት የሚችሉና ወደ 2ሺህ የሚጠጉ የአካባቢውን አርሶ አደሮች ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል፡፡

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ቦጋለ ቢፍቱ፤ የፕሮጀክቶቹ መጠናቀቅ በአካባቢው ያለውን የመልማት ዕድል በመጠቀም ያልተቆራረጠ ልማት እንዲኖር ያስችላል ብለዋል።
የልማት ዕድሎችን ለመጠቀም ጥያቄዎች ሲነሱ እንደነበር አውስተው መንግስት እያደረገ ባለው ድጋፍ ተገንብቶ የተመረቀው የወልዲያ መስኖ ፕሮጀክት ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ኑሯቸውን እንዲያሻሽሉ እድል እንደሚፈጥር ገልፀዋል፡፡

የመስኖ ፕሮጀክቱ በወቅት ሳይገደቡ በዓመት ሶስትና ከዚያ በላይ በማልማት ከራስ አልፈው ለሌላ እንዲተርፉ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ያነሱት ደግሞ ሌላኛው በሀድያ ዞን አመካ ወረዳ ነዋሪው አርሶ አደር ለራጎ መንቾሴ ናቸው፡፡

በወረዳው ድጋፍ የኤልካሜ መስኖ ፕሮጀክት ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት መደረግ የግብርና ስራቸውን በአግባቡ እንዲያለሙ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል፡፡
የመሬትና ውሃ ፀጋን በአግባቡ ለመጠቀም የመስኖ ፕሮጀክቱ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቁመው ከመኸሩ በተጨማሪ አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት የተሻለ ገቢ ለማግኘት እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

የአመካ ወረዳ ነዋሪው ርሶ አደር አየለ ኤሪሶ እንደገለፁት፤ አካባቢው ለም መሬት በመሆኑ የተለያዩ ምርቶችን ማምረት የሚያስችል መሆኑን አንስተዋል።
የአመካ መስኖ ፕሮጀክት መገንባት ከሚያመርቱት የስንዴና የጤፍ ምርት በተጨማሪ የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ በማምረት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪና የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ(ዶ/ር)፤ በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተለይም የመስኖ እድሎችን በስፋት የመጠቀም ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
ለዚህም ስኬት በሀድያና ምስራቅ ጉራጌ ዞኖች 545 ሄክታር መሬት የማልማት አቅም ያለውና በዞኖቹ ከ1ሺህ 980 በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሶስት የመስኖ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ለአገልግሎት በቅተዋል ብለዋል፡፡
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026