
ባህርዳር፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የተገኘውን ሰላም በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕስ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
የክልሉ የመንግስት አመራር አባላት በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ ላይ በባርዳር ከተማ የውይይት መድረክ እያካሄዱ ነው።
ዛሬ በተጀመረው የውይይት መድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የተከናወነው የህግ የበላይነት የማስከበር ተግባር ውጤታማ ነው።
በዚህም ሰላምን በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸው፤ ይህም መሰረተ ልማትን በመገንባት፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን በማከናወን እንደሆነ አስታውቀዋል።
በቀጣይም የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እስካሁን ሲያከናውኑ ከቆዩት በላቀ ደረጃ በቁርጠኝነት መትጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ፅንፈኛውን ቡድን ከክልሉ በማፅዳት ልማትን በዘላቂነት የማስቀጠሉ ተግባር መጠናከሩን ተናግረዋል።
በክልሉ የፀናውን ሰላም በማስቀጠል የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ለማጎልበት በየደረጃው ያለው አመራር አበክሮ መስራት እንዳለበት አሳሰበዋል።
በውይይት መድረኩ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እየተሳተፉ ነው።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026