
ባህርዳር፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የተገኘውን ሰላም በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕስ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
የክልሉ የመንግስት አመራር አባላት በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ ላይ በባርዳር ከተማ የውይይት መድረክ እያካሄዱ ነው።
ዛሬ በተጀመረው የውይይት መድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የተከናወነው የህግ የበላይነት የማስከበር ተግባር ውጤታማ ነው።
በዚህም ሰላምን በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸው፤ ይህም መሰረተ ልማትን በመገንባት፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን በማከናወን እንደሆነ አስታውቀዋል።
በቀጣይም የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እስካሁን ሲያከናውኑ ከቆዩት በላቀ ደረጃ በቁርጠኝነት መትጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ፅንፈኛውን ቡድን ከክልሉ በማፅዳት ልማትን በዘላቂነት የማስቀጠሉ ተግባር መጠናከሩን ተናግረዋል።
በክልሉ የፀናውን ሰላም በማስቀጠል የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ለማጎልበት በየደረጃው ያለው አመራር አበክሮ መስራት እንዳለበት አሳሰበዋል።
በውይይት መድረኩ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እየተሳተፉ ነው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026