የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያን የውሀ ሀብት በአግባቡ ማስተዳደር የሚያስችል ስትራቴጂክ ዕቅድ እየተዘጋጀ ነው -የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር

May 13, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ያለውን የውሀ ሃብት በአግባቡ ለይቶ ለሚያስፈልገው ጥቅም ለማዋልና ለማስተዳደር እንዲቻል የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።


ሚኒስቴሩ ረቂቅ የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀዋሳ እየመከረ ነው።


በምክክር መድረኩ ላይ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ እንዳሉት፥ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ያለንን የውሃ ሃብት በአግባቡ ለማስተዳደርና ለመጠቀም እንዲቻል የሚያግዝ ነው።


ስትራቴጂክ ዕቅዱ ምን ያህል መጠንና ጥራት ያለው የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ውሃ እንደሚገኝ፤ ለምን አገልግሎት ጥቅም ላይ መዋል እንደሚችል በመለየት በአግባቡ ማስተዳደር ያስችላል ብለዋል።


የህዝብ ቁጥሩ እየጨመረ በመጣ ቁጥር ያለን የውሃ መጠን እንዳይቀንስ የውሀ አስተዳደራችንን ማሻሻል ያስፈልጋል ያሉት አቶ ሞቱማ፥ የውሀ አጠቃቀምና አስተዳደራችንን ለማሻሻል የተዘጋጀው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ነው ያሉት።


በሚኒስቴሩ የተቀናጀ ውሃ ሃብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ በበኩላቸው፥ የውሃ ሃብቱ ዘላቂ እንዲሆን የተፋሰስ ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ትኩረት ተሰጥቷቸው መከናወናቸው የሚበረታታ ነው።


የተቀናጀ የውሃ ሃብት ልማት አስተዳደር በመዘርጋት ዘላቂነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል።


የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅዱ ዝግጅት አስተባባሪ አለልኝ ዘሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከ122 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የገጸና ከርሰ ምድር ውሃ ሃብት እንዳለ አመልክተዋል።


በትክክል ምን ያህል የውሃ ሃብት እንዳለ ለይቶ ለመረዳት የስትራቴጂክ ዕቅዱ ፋይዳው የላቀ መሆኑን አመልክተው፥ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ኢትዮጵያ ያላትን ሃብትና ሽፋን፣የውሃ ጥራት፣ተጠቃሚዎቹና ውሃው ካለበት ወደ ሌለበት ለመውሰድ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ የተሟላ መረጃ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።


በውይይት መድረኩ ላይም ከሁሉም ክልሎች የውሀ፣ ኢነርጂና ማዕድን ቢሮ ተወካዮች፣የውሃ ዘርፍ የዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026