
ሀዋሳ፤ግንቦት 4/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ያለውን የውሀ ሃብት በአግባቡ ለይቶ ለሚያስፈልገው ጥቅም ለማዋልና ለማስተዳደር እንዲቻል የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅድ እየተዘጋጀ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ረቂቅ የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሀዋሳ እየመከረ ነው።
በምክክር መድረኩ ላይ በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ እንዳሉት፥ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ያለንን የውሃ ሃብት በአግባቡ ለማስተዳደርና ለመጠቀም እንዲቻል የሚያግዝ ነው።
ስትራቴጂክ ዕቅዱ ምን ያህል መጠንና ጥራት ያለው የከርሰ ምድርና ገጸ ምድር ውሃ እንደሚገኝ፤ ለምን አገልግሎት ጥቅም ላይ መዋል እንደሚችል በመለየት በአግባቡ ማስተዳደር ያስችላል ብለዋል።
የህዝብ ቁጥሩ እየጨመረ በመጣ ቁጥር ያለን የውሃ መጠን እንዳይቀንስ የውሀ አስተዳደራችንን ማሻሻል ያስፈልጋል ያሉት አቶ ሞቱማ፥ የውሀ አጠቃቀምና አስተዳደራችንን ለማሻሻል የተዘጋጀው ስትራቴጂክ ዕቅድ ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ነው ያሉት።
በሚኒስቴሩ የተቀናጀ ውሃ ሃብት አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ደፈርሶ በበኩላቸው፥ የውሃ ሃብቱ ዘላቂ እንዲሆን የተፋሰስ ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራና የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራ ትኩረት ተሰጥቷቸው መከናወናቸው የሚበረታታ ነው።
የተቀናጀ የውሃ ሃብት ልማት አስተዳደር በመዘርጋት ዘላቂነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባም ጠቁመዋል።
የተፋሰስ መረጃ ክትትል ስትራቴጂክ ዕቅዱ ዝግጅት አስተባባሪ አለልኝ ዘሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ ከ122 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ በላይ የገጸና ከርሰ ምድር ውሃ ሃብት እንዳለ አመልክተዋል።
በትክክል ምን ያህል የውሃ ሃብት እንዳለ ለይቶ ለመረዳት የስትራቴጂክ ዕቅዱ ፋይዳው የላቀ መሆኑን አመልክተው፥ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ኢትዮጵያ ያላትን ሃብትና ሽፋን፣የውሃ ጥራት፣ተጠቃሚዎቹና ውሃው ካለበት ወደ ሌለበት ለመውሰድ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ የተሟላ መረጃ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጸዋል።
በውይይት መድረኩ ላይም ከሁሉም ክልሎች የውሀ፣ ኢነርጂና ማዕድን ቢሮ ተወካዮች፣የውሃ ዘርፍ የዩኒቨርሲቲ ምሁራንና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026