
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025 ፎረም ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና በኢትዮጵያ ያሉ ሰፊ ዕድሎችን በማስተዋወቅ በኩል ስኬታማ ስራ መከናወኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025 ፎረም ተጠናቋል።

በመድረኩ በመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎች እና ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በፎረሙ ከበርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢንቨስት ማድረግ የሚያስችል ውይይትና መግባባት መፈጠሩ ተገልጿል።
በዚሁ መሰረትም አምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መጀመር የሚያስችላቸውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር ተፈራርመዋል።
ኩባንያዎቹ በማዕድንና ሌሎችም ዘርፎች ኢንቨስት እንደሚያደርጉ ተነግሯል።
የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፎረሙ ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሀገር መሆኗ ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል።
ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና በኢትዮጵያ ያሉ ሰፊ እድሎችን በማስተዋወቅ በኩል ስኬታማ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ይዞ የመጣቸው እድሎች ላይ በቂ ግንዛቤ መፈጠሩን ተናግረው፤ በቀጣይም በዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በበኩላቸው ፎረሙ የታለመለትን ዓላማ ያሳካ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘርፉ እድገት የሚያግዙ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችም በመድረኩ በስፋት ማስተዋወቅ መቻሉን አንስተዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026