የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በፎረሙ ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና በኢትዮጵያ ያሉ ሰፊ ዕድሎችን በማስተዋወቅ በኩል ስኬታማ ስራ ተከናውኗል - ሚኒስትር አህመድ ሽዴ

May 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 5/2017(ኢዜአ)፦ በኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025 ፎረም ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና በኢትዮጵያ ያሉ ሰፊ ዕድሎችን በማስተዋወቅ በኩል ስኬታማ ስራ መከናወኑን የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ገለጹ፡፡

በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፣ በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአጋር የልማት ድርጅቶች አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው ኢንቨስት ኢትዮጵያ 2025 ፎረም ተጠናቋል።


በመድረኩ በመንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ባሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎች እና ምቹ ሁኔታዎች ዙሪያ ገለጻና ማብራሪያ ተሰጥቷል።

በፎረሙ ከበርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢንቨስት ማድረግ የሚያስችል ውይይትና መግባባት መፈጠሩ ተገልጿል።

በዚሁ መሰረትም አምስት ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ 1 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት መጀመር የሚያስችላቸውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር ተፈራርመዋል።

ኩባንያዎቹ በማዕድንና ሌሎችም ዘርፎች ኢንቨስት እንደሚያደርጉ ተነግሯል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ፎረሙ ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት ምቹ ሀገር መሆኗ ግንዛቤ የተፈጠረበት መሆኑን ገልጸዋል።

ኢንቨስትመንትን በመሳብ እና በኢትዮጵያ ያሉ ሰፊ እድሎችን በማስተዋወቅ በኩል ስኬታማ ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።

የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢንቨስትመንት ዘርፍ ይዞ የመጣቸው እድሎች ላይ በቂ ግንዛቤ መፈጠሩን ተናግረው፤ በቀጣይም በዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን የመፍጠር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።


የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን(ዶ/ር) በበኩላቸው ፎረሙ የታለመለትን ዓላማ ያሳካ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ ለዘርፉ እድገት የሚያግዙ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ ማሻሻያዎችም በመድረኩ በስፋት ማስተዋወቅ መቻሉን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026