
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2017(ኢዜአ)፦ የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ እየተገበረች የምትገኘውን የኢኮኖሚ ሪፎርም ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን የባንኩ የኢትዮጵያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን እና ኤርትራ የሰው ሀብት ልማት ፕሮግራም መሪ ሼሪን ቫርኪይ (ዶ/ር) ገለጹ።
ሼሪን ቫርኪይ (ዶ/ር) ባንኩ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተጀመረውን የሪፎርም ጉዞ ውጤታማ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ሪፎርሙ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት እና ምርታማነት የበኩሉን ሚና እንደሚወጣም አመልክተዋል።
መንግስት በማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ምቹ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ሁኔታ ለመፍጠር ያሳየውን ቁርጠኝነት ያደነቁ ሲሆን ከኢኮኖሚው ውጪ በተለያዩ መስኮች የተደረጉ ማሻሻያዎችም መልካም የሚባሉ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በኢትዮጵያ ከፍተኛ እድገት እያሳዩ ያሉ ዘርፎች እንዳሉ የገለጹት የፕሮግራም መሪው ዘርፎቹ የተሻለ ጥራት ያለው እድገት በማምጣት የኢኮኖሚ ሽግግሩን የመደገፍ ቁልፍ ሚና አላቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የአመራር ዘመን በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ማዕቀፍ ሁሉን አቀፍ ሪፎርሞችን አድርጋለች።
የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን ተከትሎም የገቢ መጠን እና የወጪ ንግድ እድገት ያሳየ ሲሆን የውጭ ምንዛሬ ክምችቱም ከሁለት እጥፍ በላይ ጨምሯል። የዋጋ ንረቱም እየቀነሰ ይገኛል።
የቴሌኮሙኒኬሽን፣ ሎጅስቲክስ፣ ኢነርጂ፣ ባንክና ሌሎችም ለውጭ ባለሀብቶች ቁልፍ የሆኑ ዘርፎች የባለሀብቶችን ቀልብ የሳቡ ናቸው።
የሪፎርም ኢኒሼቲቮቹን ያደነቁት ሼሪን ቫርኪይ (ዶ/ር) የግሉ ዘርፍ በኢንቨስትመንት እና ንግድ ያለውን ተሳትፎ የሚያሳድጉ ሪፎርሞችን በዘላቂነት ማከናወን እንደሚገባም አመልክተዋል።
በዚህ ረገድም የዓለም ባንክ ከሌሎች የልማት አጋሮች ጋር በመሆን የግሉ ዘርፍ ኢንቨስትመንት ተሳትፎ እንዲያድግ እና የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አካል እንዲሆን እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።
በልማት ፕሮግራም ላይ ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ልምድ ያላቸው ፕሮግራም መሪው በሰው ሀብት ልማት ላይ መዋዕለ ንዋይን ማፍሰስ እንደሚገባም ገልጸዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026