የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በዞኑ የማር ምርት የገበያ ትስስርን በማጠናከር በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቷል

May 16, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፡-በኢሉአባቦር ዞን የማር ምርት የገበያ ትስስርን በማጠናከር በዘርፉ የተሰማሩ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ትኩረት መስጠቱን የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ገለጹ።

''ያሉንን እምቅ የተፈጥሮ ሀብቶቻችንን ወደ ኢኮኖሚ በመቀየር ተጠቃሚነታችንንና እድገታችንን እናረጋግጥ'' በሚል መሪ ሃሳብ የማር ምርት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በመቱ ከተማ ተከፍቷል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በዞኑ ከለውጡ በፊት የማር ምርት በአብዛኛው በባሕላዊ ዘዴ ላይ የተመሰረተ ነበር።


ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዘመናዊ ቀፎ አቅርቦት እንዲሁም የነበረውን የሙያ እና የክህሎት ክፍተት አሟልቶ ወደ ስራ ተገብቷል ብለዋል።

በዚህም ባለፉት ሶስት ዓመታት ብቻ በዞኑ 330 ሺህ ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን ለአርሶ አደሩ በማቅረብ የማር ምርት ማሳደግ መቻሉንም ገልጸዋል።

የዞኑን ማር የማምረት አቅም አሟጦ ወደ ስራ በማስገባት ለዜጎች የስራ እድል መፈጠሩን ጠቅሰው ከዘርፉ የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።

በተለይም በዞኑ የሚገኙ ማር አምራች አርሶ አደሮች ጠንካራ የገበያ ትስስር ተፈጥሮላቸው ተጠቃሚነታቸው እንዲያድግ ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።


የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ በክልሉ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ትላልቅ የግብርና ልማት ኢኒሼቲቮች እየተተገበሩ መሆኑን አስታውሰዋል።

የማር ምርት ኢኒሼቲቭ በክልሉ መተግበር ከተጀመረ ወዲህ ዜጎች ከዘርፉ ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቅሰው የማር ምርት መጠንና ጥራት በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻል ማሳየቱን ተናግረዋል።

በክልሉ ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ሁሉንም አቅም በማቀናጀት ትልቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ በብልጽግና ፓርቲ የኦሮሚያ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ነመራ ቡሊ ናቸው።

በዚህም በተለይ በግብርናው ዘርፍ ተቀርጸው በከተማና በገጠር እየተተገበሩ በሚገኙ የልማት ስራዎች አበረታች ውጤቶች እየተመዘገበባቸው መሆኑን ተናግረዋል።


''እየተመዘገቡ የሚገኙ ውጤቶችም መስራት የምንችል መሆኑንና አሁንም ብዙ መስራት የሚጠበቅብን መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው'' ብለዋል።

በቀጣይ የማር ምርት መጠንና ጥራትን ለመጨመር የኤክስቴንሽንና ሙያ ድጋፍ፣ የቀፎና ተያያዥ ግብዓቶች አቅርቦት እና የገበያ ትስስር ጉዳዮች ትኩረት ሊሰጣቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ ከሁሉም ማር አምራች የኢሉአባቦር ዞን ወረዳዎች የመጡና በማር፣ በንብ ማነብና ምርት የተሰማሩ ግለሰቦችና ማህበራትን ጨምሮ የማር ነጋዴዎችና ሸማቾች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026