የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በከተማዋ ሰላምን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል - አቶ ጎሹ እንዳላማው

May 19, 2025

IDOPRESS

ባህርዳር፤ ግንቦት 9/2017(ኢዜአ)፡- በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ሰላምን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን የሕዝቡን ተጠቃሚነት የሚያጎለብቱ የተለያዩ የልማት ስራዎች መከናወናቸውን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።

በከተማው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ49 ሽህ 300 ለሚበልጡ ሰዎች የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉም ተመልክቷል።

የባህር ዳር ከተማ ምክር ቤት 4ኛ ዙር፣ 29ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ባለው መድረክ ምክትል ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውን ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል።


በዚህም ሰላምን አፅንቶ ከማስጠበቅ ጎን ለጎን የተከናወኑ የልማት ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ የሚያጎለብቱ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአስፋልት ግንባታን ጨምሮ የኮሪደር ልማት፣ የከተማ ግብርና እና አረንጓዴ ልማት ምክትል ከንቲባው ከጠቀሷቸው ተግባራት መካከል ይገኙበታል።

በተጨማሪም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ለ49ሺህ 376 ሰዎች በአገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና እና በሌሎች ዘርፎች የስራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል።

የወጣቱን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ በሚካሄዱ የሰላም ግንባታና የልማት ስራዎች ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተረዋል።


የባህር ዳር ከተማ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወይዘሮ አዲስ ትርፌ፤ ህገ ወጥ ነጋዴዎች የሚፈጥሩትን የኑሮ ውድነት ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ተናግረዋል።

የምክር ቤት አባላት ስራ አስፈጻሚው ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር እያከናወነው ያለውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት እንቅስቃሴዎች በመከታተል እየደገፉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

የባህር ዳር ከተማን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል የአካባቢውን ሰላም በጋራ ተደራጅቶ በመጠበቅ እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጠል አስገንዝበዋል።

በባህር ዳር ከተማ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቃናት በሚቆየው የምክር ቤቱ ጉባኤ ልዩ ልዩ ረቂቅ ደንቦችና መመሪያዎችን እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026