
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በአፍሪካ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ለማረጋገጥ ዲጂታል ማንነት ወሳኝ መሆኑን የአይዲ ፎር አፍሪካ ሊቀ መንበር ጆሴፍ አቲክ(ዶ/ር) ገለፁ።
ዲጂታል ማንነት ላይ ያተኮረው አይዲ ፎር አፍሪካ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በመድረኩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን ጨምሮ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአይዲ ፎር አፍሪካ ሊቀ መንበር ጆሴፍ አቲክ(ዶ/ር)፣ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ ዘሚካኤል እና ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የዓለም አቀፍ ድርጅት ተወካዮች ታድመዋል።
የአይዲ ፎር አፍሪካ ሊቀመንበር ጆሴፍ አቲክ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በአፍሪካ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንን ማረጋገጥ ውዴታ ሳይሆን ግዴታ ነው።

የዛሬው ቀን የአፍሪካውያን የዲጂታል ማንነትን ለማረጋገጥ ጉዞ የምንጀምርበት አዲስ ምዕራፍ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
በጉባኤው ለልማት መታወቂያ፣ አይዲ 4 (ID4) እንቅስቃሴን በተመለከት ሁሉም የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲወጣ የምናስገነዝብበት ነው ብለዋል።
የአፍሪካ መሪዎች የዓለምን ተለዋዋጭ ነባራዊ ሁኔታ ግምት ውስጥ በማስገባት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ግንባታ ትኩረት ሰጥተው ለመስራት እንቅስቃሴ መጀመራቸውንም አመልክተዋል።
የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ሽግግርን እውን ለማድረግ ዲጂታል ማንነትን ማረጋገጥ ቅድሚያ የሚሰጠው ወሳኝ ጉዳይ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በአፍሪካ ዲጂታል ማንነት ላይ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ይህም የአፍሪካን ሁለንተናዊ ልማትና የዜጎች ኑሮ ለማሻሻል ወሳኝ ሚና እንዳለው ነው ያስታወቁት።
ይህ መድረክ የወደፊቷን ዲጂታል አፍሪካ ለማረጋገጥ ሁሉም አፍሪካዊ ማንነቱን ለማረጋገጥ ቁርጠኝነታችንን የምናሳይበት ነው ብለዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026