
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ኢኮኖሚን የሚያነቃቁና በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ሀላፊው በድሬዳዋ አስተዳደር በግንባታ ላይ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ሼዶች፣ የኮንቬንሽን ማዕከል እና በመደመር መፅሐፍ ሽያጭ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለውን ዘመናዊ ቤተ መጻህፍት ተመልክተዋል።
በአስተዳደሩ የተመለከቷቸው የልማት ፕሮጀክቶች የድሬዳዋን ኢኮኖሚ በማነቃቃት የህዝብን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጡ ገልጸው፣ በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ የለውጡ አመራር የጋራ ህብረትና መደጋገፍ እንዲሁም የነዋሪው የተቀናጀ ተሳትፎ እየተመዘገቡ ለሚገኙ አበረታች ውጤቶች መሰረታዊ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
ከልማቱ በተጨማሪ በድሬዳዋ እየተፈጠረ ያለው የጋራ ገዢ ትርክትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑንም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ በተለያዩ መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ይበልጥ ሲጠናከሩ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጉታልም ነው ያሉት።
በልማት ሥራዎች ጉብኝት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026