
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ኢኮኖሚን የሚያነቃቁና በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ሀላፊው በድሬዳዋ አስተዳደር በግንባታ ላይ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ሼዶች፣ የኮንቬንሽን ማዕከል እና በመደመር መፅሐፍ ሽያጭ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለውን ዘመናዊ ቤተ መጻህፍት ተመልክተዋል።
በአስተዳደሩ የተመለከቷቸው የልማት ፕሮጀክቶች የድሬዳዋን ኢኮኖሚ በማነቃቃት የህዝብን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጡ ገልጸው፣ በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ የለውጡ አመራር የጋራ ህብረትና መደጋገፍ እንዲሁም የነዋሪው የተቀናጀ ተሳትፎ እየተመዘገቡ ለሚገኙ አበረታች ውጤቶች መሰረታዊ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።
ከልማቱ በተጨማሪ በድሬዳዋ እየተፈጠረ ያለው የጋራ ገዢ ትርክትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑንም ተናግረዋል።
በድሬዳዋ በተለያዩ መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ይበልጥ ሲጠናከሩ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጉታልም ነው ያሉት።
በልማት ሥራዎች ጉብኝት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026