የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ የእንስሳት ዝርያን ለማሻሻል የሚያግዝ የፈሳሽ ናይትሮጅን ማምረቻ ፋብሪካ ተመረቀ

May 26, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለእንስሳት ዝርያ ማሻሻል የሚያግዝ የፈሳሽ ናይትሮጅን ፋብሪካ ተመርቆ ስራ ጀመረ።


በወላይታ ሶዶ ከተማ ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የፈሳሽ ናይትሮጂን ማምረቻ፣ ማቀነባበሪያ እና ማሰራጫ ማዕከል በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።


በምረቃው ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ የአርሶና አርብቶ አደሩን እንስሳት ዝርያ በማሻሻል ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፥ የናይትሮጅን ማምረቻ፣ ማቀነባበሪያና ማሰራጫ ማዕከሉ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።


ማዕከሉ በክልሉ ካለው የእንስሳት ሀብት ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፥ ከዚህ ቀደም ይነሳ የነበረውን የእንስሳት ዝሪያ ማዳቀያ ግብዓት ችግር እንደሚፈታም ተናግረዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ማዕከሉ በክልሉ ያለውን የእንስሳት ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የአርሶና አርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለዋል።


በተለይ የክልሉ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ተግባሩን በማሳደግ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማሳለጥም የማዕከሉ ጠቀሜታ የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይም የክልሉና የፌዴራል የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026