የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ የእንስሳት ዝርያን ለማሻሻል የሚያግዝ የፈሳሽ ናይትሮጅን ማምረቻ ፋብሪካ ተመረቀ

May 26, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለእንስሳት ዝርያ ማሻሻል የሚያግዝ የፈሳሽ ናይትሮጅን ፋብሪካ ተመርቆ ስራ ጀመረ።


በወላይታ ሶዶ ከተማ ከ63 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባ የፈሳሽ ናይትሮጂን ማምረቻ፣ ማቀነባበሪያ እና ማሰራጫ ማዕከል በክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።


በምረቃው ወቅት ርዕሰ መስተዳድሩ፥ የአርሶና አርብቶ አደሩን እንስሳት ዝርያ በማሻሻል ተጠቃሚነቱን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀው፥ የናይትሮጅን ማምረቻ፣ ማቀነባበሪያና ማሰራጫ ማዕከሉ እየተከናወኑ ካሉ ስራዎች አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።


ማዕከሉ በክልሉ ካለው የእንስሳት ሀብት ተጠቃሚ ለመሆን አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፥ ከዚህ ቀደም ይነሳ የነበረውን የእንስሳት ዝሪያ ማዳቀያ ግብዓት ችግር እንደሚፈታም ተናግረዋል።


በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ማዕከሉ በክልሉ ያለውን የእንስሳት ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የአርሶና አርብቶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያሳድጋል ብለዋል።


በተለይ የክልሉ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻል ተግባሩን በማሳደግ በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ለማሳለጥም የማዕከሉ ጠቀሜታ የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል።


በመርሃ ግብሩ ላይም የክልሉና የፌዴራል የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026