
አዲስ አበባ፤ግንቦት 25/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከመካከለኛው ምስራቅ እና የባህረ ሰላጤ ሀገራት ጋር የማስተሳሰር አገልግሎቱን እያሰፋ መምጣቱን የአየር መንገዱ የኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ረታ መላኩ ገለፁ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ግዛት ወደ ሆነችው ሻርጃህ ከተማ ትናንት አዲስ በረራ ጀምሯል።
በበረራ ማስጀመሪያ መርኃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ ሃማድ ፋሪድ አልባዳዊ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በዚህ ወቅት የአየር መንገዱ የኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ አቶ ረታ መላኩ እንዳሉት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እአአ በ1946 ወደ የመን በጀመረው በረራ ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር ያለውን ትስስር ያስጀመረ ነው።
በተባበሩት አረብ ኤምሬቶችም ከ50 አመት በፊት እአአ በ1976 ወደ አቡዳቢ በረራ ማስጀመሩንና መዳረሻውን በየጊዜው እያሰፋ መሆኑንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከመካከለኛው ምስራቅ እና የባህረ ሰላጤ ሀገራት ጋር የማስተሳሰር አገልግሎቱን እያሰፋ መምጣቱን አንስተው፤ አሁን ላይ በ13 የመካከለኛው ምስራቅ መዳረሻዎች በሳምንት 120 የሰውና የካርጎ በረራ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ከእዚህም መካከል በዱባይና ሻርጃህ በሳምንት ከ30 በላይ የበረራ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቁመዋል።
የረጅም ዘመን ታሪክ ያላትና የአለም የንግድ ማዕከል ወደ ሆነችው ሻርጃህ የተጀመረው አዲሱ በረራ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጋር ያለውን ትስስር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
አዲስ የተጀመረው በረራ የመካከለኛው ምስራቅና የአፍሪካን የንግድ፣ ቱሪዝምና የባህል ልውውጥ ትስስርን የሚያጠናክር መሆኑንም ጠቁመዋል።

የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ኤምባሲ ምክትል የሚሲዮን መሪ ሃማድ ፋሪድ አልባዳዊ በበኩላቸው፤ አዲሱ የበረራ አገልግሎት የሁለቱን ሀገራት የባህልና ህዝብ ለህዝብ ትስስር የሚያጠናክር መሆኑን ተናግረዋል።
የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች የኢትዮጵያ ዋነኛ የንግድና የኢንቨስትመንት አጋር መሆኗን አንስተው፤ አዲስ የተጀመረው የበረራ መዳረሻ የሁለቱን አገራት ኢኮኖሚያዊ ትብብር የሚያጠናክር ነው ብለዋል።
ለንግድ አዲስ በር የሚከፍትና በሁለቱ አገራት ህዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ይበልጥ የሚያስተሳስር መሆኑንም ጠቁመዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026