
ቦንጋ፤ ግንቦት 27/2017(ኢዜአ)፦ በወቅቱና በታማኝነት በመክፈል ለሀገር ልማት የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ እንደሚያጠናክሩ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ገለጹ።
"የብልጽግና ጉዟችንና የንግዱ ማኅበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ክልላዊ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት የውይይት መድረክ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል።

በውይይቱ ከተሳተፉት መካከል አቶ ሀብታሙ አሰፋ እንዳሉት የሀገርን ልማት በዘላቂነት ማስቀጠል የሚቻለው ግብርን በአግባቡ መክፈል ሲቻል ነው።
በመሆኑም በአካባቢያቸው ልማቱ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ነጋዴው ግብሩን በወቅቱና በታማኝነት መክፈል ይኖርበታል ብለዋል።
እሳቸውም ግብር የመክፈል የዜግነት ግዴታቸውን በአግባቡ እየተወጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ጌታቸው ክፍሌ ግብራቸውን በወቅቱና በታማኝነት በመክፈል ሃላፊነታቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ መንግስት ልማትን ለማጠናከርና ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አድንቀዋል።
ግብርን በዘመናዊ መንገድ መክፈል እንዲቻል ለዲጂታል የአሰራር ሥርዓት ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥም ጠይቀዋል።
በሕገወጥ ነጋዴዎች ላይ ጠንከር ያለ ቁጥጥር መደረግ አለበት ያሉት ደግሞ ሌላው የውይይቱ ተሳታፊ አቶ ሳህሌ ሰዋኮ ናቸው።
መንግስት ግብራቸውን በታማኝነት ከሚከፍሉ ነጋዴዎች ጋር እጅ ለእጅ ተያይዞ መንቀሳቀስ እንዳለበትም ጠቅሰዋል።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ነጋ አበራ በበኩላቸውቀጣይነት ያለው ሁለንተናዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ በኃላፊነት መንፈስ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል።
የውስጥ የገቢ አቅምን ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የነጋዴው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አንስተው፣ የግብር አሰባሰቡን ለማቀላጠፍ መሠረተ ልማቶችን የማስፋፋት ሥራ በቅንጅት እየተሰሩ ይገኛል ብለዋል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች መፍታት የሚቻለው ከሀዝብ በሚሰበሰብ ገቢ መሆኑን ጠቅሰዋል።
መንግስት ፍትሀዊ የንግድ ውድድርን ለማስፈን በሚያደርገው ጥረት የንግዱ ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣም አሳስበዋል።
መንግስት በሚሰበስበው ግበር በተለያዩ ዘርፎች ልማትን ለማረጋገጥ እየሰራ ይገኛልም ነው ያሉት።
በተለይ ኢኒሼቲቭ ወስዶ በየሴክተሩ ባከናወናቸው የልማት ሥራዎች አመርቂ ውጤት እየተመዘገበና ዜጎችም ተጠቃሚ እየሆኑ መምጣታቸውን ተናግረዋል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026