
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ስሎቪንያ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራን ለማጠናከር የባለሙያና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) ገለጹ።
አገሪቱ በዘመናዊ ንብ ማነብ ላይ ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማጋራት ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ ትሰራለችም ብለዋል።
በዚሁ ወቅት ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የተካሄደ ሲሆን በዚህም የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እና ልዑካቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እንዳሉት ስሎቪንያና ኢትዮጵያ መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው።
ስሎቪንያ በዘመናዊ ንብ ማነብ ልምድ ያላት አገር መሆኗንና በኢትዮጵያ ለዘርፉ የባለሙያና ቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቀዋል።
ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የዛሬ ብቻ ሳይሆን ለትውልድ የሚሻገር ፕሮጀክት ነው ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ በሌሎች መስኮችም ያለው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው የንብ ማነብና ከተማ ግብርና ስራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና አካባቢን ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅና የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስራ ከአየር ንብረት ለውጥ ስትራቴጂ ጋር የተሰናሰለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ የጋራ የልማት ግብ ካላቸው ጋር በትብብር እንደምትሰራም ገልጸዋል።
በአዲስ ዙ ፓርክ በይፋ የተጀመረው ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ የአለም አቀፍ ትብብር ማሳያ ጭምር መሆኑን ጠቅሰው፤ ለትምህርትና ለቱሪዝም ዘርፍም ጠቃሚ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026