አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2017(ኢዜአ)፦ በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ትግበራው አሳታፊና የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ መፈጠሩን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሁለተኛው ምዕራፍ 5ኛ ዙር "ስለ ኢትዮጵያ" የፓናል ውይይት" ስራ ዕድል ፈጠራ ስለ ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ሃሳብ በአዳማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ወቅት፤ በበይነ መረብ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ በተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ ሃብቶች የበለፀገች መሆኗን ተከትሎ ሃብቶቿን ጥቅም ላይ ለማዋል እየሰራች ነው ብለዋል።
በዚህም ያላትን ጸጋ በመጠቀም የክህሎት ልማትን፣ የስራ ዕድል ፈጠራንና የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነትን በማስተሳሰር አመርቂ ውጤቶችን እያስመዘገበች እንደምትገኝ ተናግረዋል፡፡
በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ትግበራው አሳታፊና የዜጎችን ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ መፍጠር መቻሉንም ገልጸዋል፡፡
ይህም ዜጎች በሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ለማጎልበት ምቹ ድል እንደሚፈጥርም አክለዋል።
በዚህ ረገድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በክህሎት ልማት ላይ ለሚያከናውነው ተግባር ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራው በእጅጉ እያገዘ ስለመሆኑም አንስተዋል።
የስራ ዕድል ፈጠራ ጉዳይ የዜጎች የህልውና ጉዳይ መሆኑን የገለፁት ሚኒስትሯ እሴት የታከለበት የስራ ዕድል ተደራሽነትን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለዚህም በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ የሀገራትን ልምድና ተሞክሮ የቀመረና አዳዲስ የስራ አማራጮችን ተደራሽ ያደረገ የስራ ዕድል ፈጠራ ትኩረት ተሰጥቶታል ብለዋል።
ይህም በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ላይ ጎልቶ የሚታይ የስራ ዕድል ተጠቃሚነትን ተደራሽ ለማድረግ አስቻይ ሁኔታ መፈጠሩን ነው የጠቀሱት።
በዘርፉ ጥቅም ላይ የዋሉ ቴክኖሎጂዎች ለክህሎት ልማት ስራ ስኬታማነት ጉልህ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልፀው በዚህም አበረታች ውጤት ተመዝግቧል ነው ያሉት።
የተመዘገቡ ውጤቶችን ከዳር ለማድረስ የፋይናንስ ስርዓቱን ተአማኒና ፍትሃዊ ማድረግ ላይ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም አንስተዋል።
እንዲሁም የግሉ ዘርፍ ተዋናዮች በስራ ዕድል ፈጠራ ላይ ያለውን አቅም አሟጦ በመጠቀም የዜጎችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥና ለአካታች ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ ማጉላት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025