የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በጉጂ ዞን በመስኖ ከለማው መሬት ከ1 ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአትክልትና ስራስር ምርት ተሰብስቧል

Jun 11, 2025

IDOPRESS

ነገሌ ቦረና፣ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦በጉጂ ዞን በመስኖ ከለማው መሬት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአትክልትና ስራስር ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡

በዞኑ ከነሀሴ አጋማሽ እስከ ታህሳስ መጨረሻ የመጀመሪያው ዙር ከየካቲት መጀመሪያ እስከ ግንቦት መጨረሻ 2ኛ ዙር የመስኖ ልማት ወቅት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡

የጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ፤ በዞኑ በ2ኛው ዙር የመስኖ ስራ 12 ሺህ 78 ሄክታር መሬት መልማቱን ገልጸዋል፡፡

ከዚህም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት በመሰብሰብ ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፥ እስካሁን በተካሄደው ስራም ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአትክልትና ስራስር ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡

በመስኖ ከለሙት የአትክልትና ስራስር አይነቶች መካከል ድንች፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጎመን፣ ቃሪያ፣ ካሮት፣ ቀይ ስርና ሰላጣ የመሳሰሉትን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡

ምርቱን ለማሳደግ 43 ሺህ 91 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮና 1 ሺህ 626 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ፤16 ሺህ 803 ኩንታል ምርጥ ዘር ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቅሰዋል፡፡

በልማቱ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን 23 ሺህ 797 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡

የመስኖ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግ ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብ ባለው ሂደት የባለሙያ እገዛና ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.