
ነገሌ ቦረና፣ሰኔ 4/2017(ኢዜአ)፦በጉጂ ዞን በመስኖ ከለማው መሬት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአትክልትና ስራስር ምርት መሰብሰቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ፡፡
በዞኑ ከነሀሴ አጋማሽ እስከ ታህሳስ መጨረሻ የመጀመሪያው ዙር ከየካቲት መጀመሪያ እስከ ግንቦት መጨረሻ 2ኛ ዙር የመስኖ ልማት ወቅት እንደሆነ ተመልክቷል፡፡
የጽህፈት ቤቱ የሰብል ልማት ባለሙያ አቶ መንግስቱ ሂርባዬ፤ በዞኑ በ2ኛው ዙር የመስኖ ስራ 12 ሺህ 78 ሄክታር መሬት መልማቱን ገልጸዋል፡፡
ከዚህም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት በመሰብሰብ ለገበያ ለማቅረብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን አስታውሰው፥ እስካሁን በተካሄደው ስራም ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ የአትክልትና ስራስር ምርት መሰብሰቡን ገልጸዋል፡፡
በመስኖ ከለሙት የአትክልትና ስራስር አይነቶች መካከል ድንች፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ቲማቲም፣ ጎመን፣ ቃሪያ፣ ካሮት፣ ቀይ ስርና ሰላጣ የመሳሰሉትን ለአብነት ጠቅሰዋል፡፡
ምርቱን ለማሳደግ 43 ሺህ 91 ሜትር ኪዩብ የተፈጥሮና 1 ሺህ 626 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ፤16 ሺህ 803 ኩንታል ምርጥ ዘር ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቅሰዋል፡፡
በልማቱ ከእንስሳት እርባታ ጎን ለጎን 23 ሺህ 797 አርሶ አደሮችና ከፊል አርብቶ አደሮች መሳተፋቸውን ገልጸዋል፡፡
የመስኖ ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግ ከማሳ ዝግጅት እስከ ምርት አሰባሰብ ባለው ሂደት የባለሙያ እገዛና ድጋፍ መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026