የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ትውልድ በመቅረጽ ሂደት ውስጥ ሚና ያላቸው ተቋማት የሥራ ባህል እንዲዳብር ትውልድን የማነጽ ሚናቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል- ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Jun 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 12/2017(ኢዜአ)፦ትውልድ በመቅረጽ ሂደት ውስጥ ሚና ያላቸው ተቋማት የሥራ ባህል እንዲዳብር ትውልድን የማነጽ ሚናቸውን ሊያጠናክሩ እንደሚገባ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ።

"የስራ ባህል ምርታማነት ለሀገር ሉዓላዊነት" በሚል መሪ ሃሳብ የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ተካሄዷል፡፡


በመድረኩም የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል፣ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)፣ የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሰለሞን ሶካ፣ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ሰይፈ ደርቤ፣ የፌዴራል እና ክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት እንዳሉት፤ የስራ ባህል ግንባታ ስኬታማ እንዲሆን ትውልድን ከታች ጀምሮ መቅረጽ ይገባል፡፡

ትውልድን በመቅረጽ የሃይማኖት ተቋማት፣ ትምህርት ቤቶች ፣መገናኛ ብዙሃንን ጨምሮ የባለድርሻ አካላት ሚና የላቀ ሊሆን እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ለሙያ ያለን አመለካከት የአስተሳሰብ ለውጥ የሚፈልግ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ ከቤተሰብ ጀምሮ የስራ ባህልን የማዳበር ስራ ትኩረት እንደሚፈልግ ጠቅሰዋል፡፡

ያሉንን አቅምና ጸጋ መለየት በዚያ ላይ ተመስርቶ ፈጠራና ፍጥነትን በማከል ውጤታማ ስራ ማከናወን ይጠበቅብናል ነው ያሉት፡፡

በዚህ ረገድ እንደ አገር መልካም ጅምሮች በመኖራቸው ይህንኑ በማስፋት ለውጤት እንዲበቃ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡

ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ላይ ያሉ ባለድርሻ አካላትም ሚናቸውን ማጠናከር እንደሚገባቸውም አመልክተዋል።


የውጭ ጉዳይ ኢኒስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አብዲ ዘነበ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በኢኮኖሚ ራስን ለመቻል የተጀመረው አገራዊ ጥረት የሚሳካው ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ ሲወጣ መሆኑን አመልክተዋል።

ለዚህ ደግሞ መሰል የውይይት መድረክ ፋይዳው ብዙ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

የኢንተርፕሪነርሺፕ ልማት ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሐሰን ሁሴን (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ልምዳቸውን እና ካፒታላቸውን ወደ ኢትዮጵያ እንዲያመጡ ማድረግ ይገባል ብለዋል።


በውጭ ያሉ ዜጎች በኢትዮጵያ የሚኖራቸው ተሳትፎ ከፍ እንዲል ምቹ ሁኔታ መፍጠር ይገባል ነው ያሉት።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሥነ ሕዝብ መምህርና ተመራማሪ እሸቱ ጉርሙ(ፕሮፌሰር) እንዳሉት፤ ምርታማነትን ለማሳደግ በትምህርትና በክህሎት የበለጸገ የሰው ኃይል ማፍራት ይጠይቃል።


በእውቀትና በአስተሳሰብ የተገነባ ትውልድ ውጤታማ ነው ያሉት ተመራማሪው፤ ሙያን መሰረት ያደረጉ የሥራ ሥምሪት ጉዳዮች የበለጠ ትኩረት ይሻሉ ብለዋል።

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር አማካሪ ጥላሁን በጅቷል (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ከጠባቂነት የተላቀቀ አስተሳሰብ ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸው፤ በምርቶች ላይ እሴት መጨመር ጉዳይ ትኩረት ይፈልጋል ብለዋል።


ያሉንን ዕድሎች ተጠቅመን መለወጥ አለመቻላችን ሊያስቆጨን ይገባል ሲሉም ተናግረዋል።

በፖሊሲ ጥናት ኢኒስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ ጥላሁን ተፈራ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የተያዘው አገራዊ ግብ የሚሳካው የተረጋጋ የፖለቲካ ሥርዓት በማስፈን ውስጥ ነው።


ለዚህም እንደ መንግሥት የተጀመሩ ሥራዎችን አበረታች መሆናቸውን ገልጸው፤ መሰል ሥራዎችን ማስፋት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በምዕራብ ሸዋ ዞን የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ለንብ ማነብ ስራ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ የማር ምርት እያደገ መጥቷል

አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...

Jun 14, 2026

የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...

Jun 11, 2026

ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ ነው

ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...

Jun 1, 2026

በክልሉ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን የማብቃት ሥራው ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...

May 26, 2026