
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ ለሥራ ሥምሪት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ለሥራው በቂ እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ መንግስት ክህሎትን መሰረት ያደረገ የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው፡፡
ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ዜጎች ለውድድር የሚያበቃቸውን ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና እንዲወስዱና ሥራ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በርካታ ወጣቶች በአጭርና በረጅም ጊዜ ስልጠና ክህሎታቸውን በማዳበር በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ውጤታማ መሆን ችለዋል ብለዋል፡፡
መንግስት ለዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ እድል ከመፍጠር ባለፈ ክብራቸው ተጠብቆ ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውን እና አኗኗራቸውን በማስተዋወቅ የሀገራቸው ዲፕሎማት እንዲሆኑ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
መንግስት በውጭ አገራት የሥራ ሥምሪት የሚያገኙ ዜጎች የሀገራቸውን እሴት ማስተዋወቅ የሚችሉበት ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡
ዜጎች ባፈሩት ጥሪትና በቀሰሙት እውቀት ለራሳቸውና ለሀገራቸው የቴክኖሎጂ ሽግግር መፍጠር የሚችሉበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል፡፡
በዓለም ላይ ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በ20 ዋና ዋና ዘርፎች ለሥራ ስምሪት የሚያግዝ ስልጣነ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026