
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 15/2017(ኢዜአ)፦ ለሥራ ሥምሪት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ለሥራው በቂ እውቀትና ክህሎት እንዲኖራቸው የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ለኢዜአ እንዳሉት፤ መንግስት ክህሎትን መሰረት ያደረገ የስራ እድል ፈጠራ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው፡፡
ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ዜጎች ለውድድር የሚያበቃቸውን ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና እንዲወስዱና ሥራ እንዲያገኙ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በርካታ ወጣቶች በአጭርና በረጅም ጊዜ ስልጠና ክህሎታቸውን በማዳበር በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ውጤታማ መሆን ችለዋል ብለዋል፡፡
መንግስት ለዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ እድል ከመፍጠር ባለፈ ክብራቸው ተጠብቆ ባህላቸውን፣ ቋንቋቸውን እና አኗኗራቸውን በማስተዋወቅ የሀገራቸው ዲፕሎማት እንዲሆኑ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡
መንግስት በውጭ አገራት የሥራ ሥምሪት የሚያገኙ ዜጎች የሀገራቸውን እሴት ማስተዋወቅ የሚችሉበት ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ ስልጠና እየሰጠ ነው ብለዋል፡፡
ዜጎች ባፈሩት ጥሪትና በቀሰሙት እውቀት ለራሳቸውና ለሀገራቸው የቴክኖሎጂ ሽግግር መፍጠር የሚችሉበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል፡፡
በዓለም ላይ ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ በ20 ዋና ዋና ዘርፎች ለሥራ ስምሪት የሚያግዝ ስልጣነ ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026