አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከኮካ ኮላ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሊዩሳ ኦርቴጋ ጋር በአንጎላ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ጎን ለጎን ተወያይተዋል።
ውይይታቸውም ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ማስፋት በሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ውይይቱን የተከታተሉት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሙሌ ታረቀኝ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኮካ ኮላ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1958 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሥራውን ማከናወን መጀመሩን ጠቅሰው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል በመፍጠርና ኢኮኖሚውን በመደገፍ ላበረከተው አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል።
ኮካ ኮላ የሚጠበቅበትን ማኅበራዊ ሀላፊነት በመወጣት በኩል እያበረከተ ላለው አስተዋጽዖ አመስግነው አሁንም ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን እንዲያሰፋ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ያለው ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር፣ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና ሌሎች ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢዎች ኮካ ኮላ ኢንቨስትመንቱን እንዲያጠናክር የሚያስችሉ መሆናቸውን በውይይቱ መነሳቱን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025