
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከኮካ ኮላ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሊዩሳ ኦርቴጋ ጋር በአንጎላ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ጎን ለጎን ተወያይተዋል።
ውይይታቸውም ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ማስፋት በሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ውይይቱን የተከታተሉት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሙሌ ታረቀኝ ለኢዜአ ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ኮካ ኮላ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1958 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሥራውን ማከናወን መጀመሩን ጠቅሰው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል በመፍጠርና ኢኮኖሚውን በመደገፍ ላበረከተው አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል።
ኮካ ኮላ የሚጠበቅበትን ማኅበራዊ ሀላፊነት በመወጣት በኩል እያበረከተ ላለው አስተዋጽዖ አመስግነው አሁንም ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን እንዲያሰፋ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ያለው ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር፣ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና ሌሎች ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢዎች ኮካ ኮላ ኢንቨስትመንቱን እንዲያጠናክር የሚያስችሉ መሆናቸውን በውይይቱ መነሳቱን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።
አምቦ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሸዋ ዞን ባለፉት ዓመታት በተከናወኑ የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት ስራዎች ለንብ ማነብ ምቹ ሁኔታ በመፍጠሩ...
Jun 14, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል የበጋ መስኖ ልማት በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ የአርስ አደሩን ተጠቃሚነት እያሳደገ መሆኑን የክልሉ ምክት...
Jun 11, 2026
ሐረማያ፤ ግንቦት 20/2018 (ኢዜአ)፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን እያጎለበተ እንደሚገኝ አስታወቀ። ዩኒቨ...
Jun 1, 2026
ሆሳዕና፣ግንቦት 17/2018 (ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የሕብረት ሥራ ማህበራትን ደግፎ የማብቃት ሥራው ተጠናክሮ እ...
May 26, 2026