የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከኮካ ኮላ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሊዩሳ ኦርቴጋ ጋር ተወያዩ

Jun 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2017(ኢዜአ)፦ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ከኮካ ኮላ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሊዩሳ ኦርቴጋ ጋር በአንጎላ እየተካሄደ ባለው የአፍሪካ አሜሪካ የቢዝነስ ጉባኤ ጎን ለጎን ተወያይተዋል።

ውይይታቸውም ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ማስፋት በሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች ላይ ያተኮረ እንደነበር ውይይቱን የተከታተሉት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአውሮፓና አሜሪካ ጉዳዮች ምክትል ዳይሬክተር ጄኔራል አምባሳደር ሙሌ ታረቀኝ ለኢዜአ ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ኮካ ኮላ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ1958 ጀምሮ በኢትዮጵያ ሥራውን ማከናወን መጀመሩን ጠቅሰው ከዛ ጊዜ ጀምሮ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የሥራ ዕድል በመፍጠርና ኢኮኖሚውን በመደገፍ ላበረከተው አስተዋጽዖ ምስጋና አቅርበዋል።

ኮካ ኮላ የሚጠበቅበትን ማኅበራዊ ሀላፊነት በመወጣት በኩል እያበረከተ ላለው አስተዋጽዖ አመስግነው አሁንም ኩባንያው በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን እንዲያሰፋ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ያለው ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር፣ የመሰረተ ልማት መስፋፋትና ሌሎች ምቹ የኢንቨስትመንት ከባቢዎች ኮካ ኮላ ኢንቨስትመንቱን እንዲያጠናክር የሚያስችሉ መሆናቸውን በውይይቱ መነሳቱን ኢዜአ ከስፍራው ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026

በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል የመሰረተ ልማት ግንባታ እየተከናወነ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...

Mar 31, 2026