አዲስ አበባ፤ ሰኔ 18/2017 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ውስጥ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ከፍተኛ እምርታ ማስመዝገቧን የዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት አስታወቀ።
የዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት (ITU) የአፍሪካ ቀጣና ዳይሬክተር ኢማኑኤል ማናሴህ ኢትዮጵያ የዲጂታል ስትራቴጂ በመቅረጽ እና በመተግበር የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማምጣት እያከናወነች ያለውን ስራ የሚደነቅ መሆኑን ከኢዜአ በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።
ዓለም አቀፍ ትስስር እና ዘላቂ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን የህብረቱ ስትራቴጂካዊ ግቦች ናቸው ያሉት ዳይሬክተሩ ኢትዮጵያም የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ ላይ ከፍተኛ ለውጥ ማምጣቷን አመልክተዋል።
ህብረቱ በኢትዮጵያ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እቅድ ቀረጻ እና ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል።
ቀጣናዊ ዳይሬክተሩ የኦንላይን ትስስር የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዋንኛ የልብ ትርታ መሆኑን ጠቅሰው ዲጂታላይዜሽንን እውን ለማድረግ የሚያስችል መሰረት ነው ብለዋል።
በዚህ ረገድም ኢትዮጵያ የዲጂታል አድማስን በማስፋት አስደናቂ ስራ ማከናወኗን ነው የገለጹት።
በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ዲጂታል አገልግሎቶች አማካኝነት የቴሌብር ተጠቃሚዎች ቁጥርን በአጭር ጊዜ ከ50 ሚሊዮን በላይ ማድረስ ትልቅ ስኬት ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን መጻኢ ጊዜ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና ኢኔቬሽን ስራዋ ውስጥ እያየን ነው ብለዋል።
የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ ለዲጂታል ልማት በተጨባጭ የሰጠችውን ትኩረት በግልጽ እንደሚያመላክትም ነው ያብራሩት።
ዓለም አቀፉ የቴሌኮም ህብረት እ.አ.አ በ1865 የተቋቋመ አንጋፋ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ልዩ ኤጀንሲ ነው።
ተቀማጭነቱን በስዊዘርላንዳድ ጄኔቫ ያደረገው ህብረቱ ከኢንፎርሜሽን እና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂዎች ጋር የተያያዙ ስራዎችን በዋናነት ያከናውናል።
ዓለም አቀፍ ተቋሙ ኢትዮጵያን ጨምሮ 194 አባል ሀገራት አሉት።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025